ና ፡ ጌታ (Na Gieta) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

፲ ፭ (15)

ርዝመት (Len.): 3:42
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

ሕዝብህ ፡ ይጠብቅሃል ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
መገለጥህ ፡ ናፍቆታል ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
እባክህ ፡ ናልኝ ፡ ሳትቆይ ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
ጊዜው ፡ አልደረሰም ፡ ወይ ? ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!

አዝና ፡ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ! (፫x)
ጊዜው ፡ አልደረሰም ፡ ወይ?

ስምህን ፡ ስለወደደች ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
ነፍሴ ፡ ስድብን ፡ ጠገበች፡ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታዬ ፡ ሆይ!
ባርኮቷን ፡ እያሰበች፡ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
ዛሬም ፡ በአንተ ፡ ታምናለች፡ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!

አዝና ፡ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ! (፫x)
ጊዜው ፡ አልደረሰም ፡ ወይ?

ድካሙ ፡ ሳይበረታ ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
አርበኛው ፡ ሳይረታ፡ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
የተጋዳይ ፡ አለኝታ ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
በጠላትህ ፡ ላይ ፡ በርታ ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!

አዝና ፡ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ! (፫x)
ጊዜው ፡ አልደረሰም ፡ ወይ?

ጣኦቱ ፡ ተሰባብሮ ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
ልመልከት ፡ ስምህ ፡ ከብሮ ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
ከጥንት ፡ እንደታወቅህ ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!
ምድር ፡ አንተን ፡ ትወቅ ፣ ና ፣ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ!

አዝና ፡ ጌታዬ ፣ ጌታ ፡ ሆይ! (፫x)
ጊዜው ፡ አልደረሰም ፡ ወይ?