እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት (Endetekebelkut Meheret) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 5:06
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት

እስራቴን ፡ ቆርጠህ ፡ ቀንበሬን ፡ ሰብረሃል
ነፍሴ ፡ እንድታከብርህ ፡ ነጻ ፡ አውጥተኸኛል
ባርነት ፡ አበቃ ፡ ልጅ ፡ ነህ ፡ ብለኸኛል
በደምህ ፡ ቃልኪዳን ፡ የአንተ ፡ አድርገኸኛል

አዝ፦ እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት

የተፍገመገመ ፡ ከውድቀት ፡ እንዲተርፍ
የደከመን ፡ ሁሉ ፡ በቃልህ ፡ እንድደግፍ
አንቃኝ ፡ በማለዳ ፡ ቀስቅሰኝ ፡ ከእንቅልፍ
ታማኝ ፡ ሎሌ ፡ አድርገኝ ፡ ልብን ፡ የሚያሳርፍ

አዝ፦ እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት

ስንፍናዬን ፡ አርቅ ፡ በተግሳፅህ ፡ በትር
እንድተጋ ፡ እርዳኝ ፡ ከፀጋህ ፡ ዙፋን ፡ ሥር
ኢየሱስ ፡ ያድናል ፡ ብዬ ፡ እንድመሰክር
ሕይወቴን ፡ ሙላልኝ ፡ በመስቀልህ ፡ ፍቅር

አዝ፦ እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት

ጥበብ ፡ ለሌላቸው ፡ ለማያስተውሉ
ለተማሩም ፡ ሰዎች ፡ አውቀናል ፡ ለሚሉ
ወንጌሉን ፡ ልናገር ፡ እንዲድኑ ፡ አምነው
ለእነዚህ ፡ ሁሉ ፡ ዕዳዬ ፡ ትልቅ ፡ ነው

አዝ፦ እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት

ወንጌል ፡ አይቆጠብ ፡ አይወሰን ፡ በክልል
እስከ ፡ ምድር ፡ ዳር ፡ ይሂድ ፡ ቃልህ ፡ ሳይከለከል
ለቅርቡ ፡ ለሩቁ ፡ ጽድቅህም ፡ ይታደል
የሱስን ፡ አግኝቶ ፡ ፍጥረት ፡ እሰይ ፡ ይበል

አዝ፦ እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት