እጁን ፡ ዘርግቶ (Ejun Zergeto) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 3:36
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የሞትንስ ፡ ፍርድ ፡ ብዙ ፡ ጊዜ ፡ ሰምተናል
በሕይወት ፡ ለመኖር ፡ ዕለት ፡ ዕለት ፡ ሞተናል
የኢየሱስን ፡ ሞት ፡ ተሸክመን ፡ ዞረናል
በዚህ ፡ ሁሉ ፡ ግን ፡ በምህረቱ ፡ ኖረናል

አዝ፦ እጁን ፡ ዘርግቶ ፡ ጌታ ፡ ባይረዳን ፡ ከእኛ ፡ ጋር ፡ ሆኖ
በችግራችን ፡ ባይታደገን ፡ እንደዚህ ፡ ፈጥኖ
ረግረጉ ፡ ውጦን ፡ ልንጠፋ ፡ ነበር ፡ ውኃ ፡ አስጥሞን
ዛሬ ፡ ግን ፡ ድነን ፡ በሕይወት ፡ አለን ፡ ኢየሱስ ፡ አውጥቶን

በእምነት ፡ እንጂ ፡ በምናየው ፡ አይደለም
ከጌታ ፡ በቀር ፡ እኛ ፡ ትምክህት ፡ የለንም
ጽድቃችን ፡ እንኳን ፡ ለዚህ ፡ አላበቃንም
ፀጋው ፡ አጽንቶን ፡ ከርሱ ፡ አልተለየንም

አዝ፦ እጁን ፡ ዘርግቶ ፡ ጌታ ፡ ባይረዳን ፡ ከእኛ ፡ ጋር ፡ ሆኖ
በችግራችን ፡ ባይታደገን ፡ እንደዚህ ፡ ፈጥኖ
ረግረጉ ፡ ውጦን ፡ ልንጠፋ ፡ ነበር ፡ ውኃ ፡ አስጥሞን
ዛሬ ፡ ግን ፡ ድነን ፡ በሕይወት ፡ አለን ፡ ኢየሱስ ፡ አውጥቶን

ሕያዋን ፡ ሆነን ፡ በእርሱ ፡ እንኖራለን
የጌታን ፡ ሥራ ፡ ዛሬም ፡ እንገልጻለን
ክብር ፡ ለሥሙ ፡ ሞገስ ፡ ለሥሙ ፡ ብለን
ያለንን ፡ ሁሉ ፡ ለእርሱ ፡ እንሰዋለን

አዝ፦ እጁን ፡ ዘርግቶ ፡ ጌታ ፡ ባይረዳን ፡ ከእኛ ፡ ጋር ፡ ሆኖ
በችግራችን ፡ ባይታደገን ፡ እንደዚህ ፡ ፈጥኖ
ረግረጉ ፡ ውጦን ፡ ልንጠፋ ፡ ነበር ፡ ውኃ ፡ አስጥሞን
ዛሬ ፡ ግን ፡ ድነን ፡ በሕይወት ፡ አለን ፡ ኢየሱስ ፡ አውጥቶን