አምላኬ ፡ አምላኬ (Amlakie Amlakie) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 4:43
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝአምላኬ (፪x) ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ እገሰግሳለሁ
ኃይልህን ፡ ክብርህን ፡ እንዳይ ፡ እሮጣለሁ
ፊትህን ፡ አሳየኝ ፡ ደስታን ፡ እጠግባለሁ
ምህረትህ ፡ ይብዛልኝ ፡ በሕይወት ፡ እኖራለሁ

ገና ፡ ሌሊት ፡ ሳለ ፡ ከእንቅልፌ ፡ እነሳለሁ
የፊትህን ፡ ብርሃን ፡ ላይ ፡ እፈልጋለሁ
ነፍሴ ፡ እንደ ፡ ውኃ ፡ አንተን ፡ ትጠማለች
በቀንም ፡ በማታም ፡ ትናፍቅሃለች

አዝአምላኬ (፪x) ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ እገሰግሳለሁ
ኃይልህን ፡ ክብርህን ፡ እንዳይ ፡ እሮጣለሁ
ፊትህን ፡ አሳየኝ ፡ ደስታን ፡ እጠግባለሁ
ምህረትህ ፡ ይብዛልኝ ፡ በሕይወት ፡ እኖራለሁ

እጆቼን ፡ በሥምህ ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ እያነሳሁ
በዘወትር ፡ ፀሎት ፡ ምሥጋና ፡ አቀርባለሁ
በሁለንተናዬም ፡ እገዛልሃለሁ
ምንጊዜም ፡ የአንተው ፡ ነኝ ፡ በቤትህ ፡ እኖራለሁ

አዝአምላኬ (፪x) ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ እገሰግሳለሁ
ኃይልህን ፡ ክብርህን ፡ እንዳይ ፡ እሮጣለሁ
ፊትህን ፡ አሳየኝ ፡ ደስታን ፡ እጠግባለሁ
ምህረትህ ፡ ይብዛልኝ ፡ በሕይወት ፡ እኖራለሁ

ሺህ ፡ ዓመት ፡ በሥጋ ፡ ከመኖር ፡ በከንቱ
እውነትህን ፡ አውቆ ፡ ይሻላል ፡ መሞቱ
መስቀልህን ፡ መያዝ ፡ መርጫለሁ ፡ እኔ
ይህ ፡ ነው ፡ ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ የነፍሴ ፡ ውሳኔ

አዝአምላኬ (፪x) ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ እገሰግሳለሁ
ኃይልህን ፡ ክብርህን ፡ እንዳይ ፡ እሮጣለሁ
ፊትህን ፡ አሳየኝ ፡ ደስታን ፡ እጠግባለሁ
ምህረትህ ፡ ይብዛልኝ ፡ በሕይወት ፡ እኖራለሁ