From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አንተ ባለህበት በከበረው ስፍራ
ካንተ ጋራ ልኖር ስምህን እንድጠራ
እድሉን አገኘው በቤትህ ልቀድስ
እጥፍ ልስገድልህ ነፍሴን ፊትህ ላፍስስ
እንዴት መታደል ነው ስምህን መጥራቱ
ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ማለቱ
የተመረጠ ስም ከስም ሁሉ በላይ
አይኔን አድርጎታል ካንተ ሌላ እንዳላይ
የህይወቴ ኢየሱስ ጌታ ነህ
ኢየሱስ የኑሮዬ ኢየሱስ ንጉስ ነህ
ኢየሱስ መአዛህን ኢየሱስ ስወደው
ኢየሱስ መገኘትህ ኢየሱስ ህይወቴ ነው
ኢየሱስ ኢየሱስ ወደድኩህ
ከእልፍ ከአእላፋት መረጥኩህ
ውዴ ከእንቁ ትበልጣለህ
ከማር ወለላ ትጣፍጣለህ
እረ እንዴት እድለኛ ነኝ
በፊትህ ሞገስን አገኘሁኝ
የኔ ብቻ አይበቃም ዝማሬ
ይገዛልህ ዘር ማንዘሬ
የቤትህ ስርአት በሚደረግበት
ህዝቡም መላእክቱም ቅዱስ በሚሉበት
እድሉን አገኘው ዘላለም ላመልክህ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያልኩ ከቅዱሳንህ
እንዴት መታደል ነው ዘላለም ማምለኬ
ጎንበስ ቀና እያልኩ ፊትህ ተንበርክኬ
በማይነገር ክብር በሚደነቅ ብርሃን
ላይህ ጉዋጉቻለው ውዴ ኢየሱስ አንተን
ኢየሱስ ሙሽራዬ ኢየሱስ ቶሎ ና
ኢየሱስ መናፈቄ ኢየሱስ በዝትዋልና
ኢየሱስ ማዶ ማዶ ኢየሱስ ማዶ እያየው
ኢየሱስ አማትሬ ኢየሱስ እጠብቅሃለው
|