አመለጠች ነፍሴ (Ameletech Nefse) - ሳሙኤል ተስፋሚካአኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ተስፋሚካአኤል
(Samuel Tesfamichael)

Lyrics.jpg


(4)

መልህቄ
(Melhike)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ ፬ (2022)
ቁጥር (Track):

፲ ፮ (16)

ርዝመት (Len.): 6:41
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ተስፋሚካአኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Tesfamichael)

እግዚአብሔር ባይራራልኝ
ልጁን ልኮ ባይታደገኝ
የጠላት ሴራ ወጥመድ ዘርግቶብኝ
በሙታን ሰፈር እዛው ላይ በቀረሁኝ

ግን አልተሳካም አልሆነለትም
ነፍሴ ከቶ አላገኛትም
በክርስቶስ በተሰራው ስራ
አመለጠች እንደወፍ በራ

አመለጠች/4
ነፍሴ እንደወፍ ከአዳኞች ወጥመድ አመለጠች

በርራ በርራ እንደ ወፍ በርራ /2
አመለጠች በርራ /2
በክርስቶስ ስራ
አመለጠች በርራ
በመስቀል ላይ ስራ
አመለጠች በርራ

አዳኙ በስውር ወጥመድ አስቀመጠ
ከአሁን አሁን ያዘልኝ ሲል አይኑ እንዳፈጠጠ
አዳኜ ሲመጣ ወጥመዱን ሲረግጠው
ነፍሴን አስመልጦ ቀንበሩን ሰባበረው /4

እንዲህን ነው ያመለጠችው ነፍሴ/2
እንደወፍ አመለጠች ነፍሴ /2
በረረች አመለጠች ነፍሴ /2
በአዳኝዋ በኢየሱሴ/4
በኢየሱሴ

ሞትና ሲኦል አንድ ላይ ተስማምተው
ዘላለሜን ሊያደርጉት በድቅድቅ ጨለማው
የትንሳኤው ጉልበት ሞትን ራሱን ገድሎት
መውጊያውን ሰባብሮ ነፍሴ አስመለጣት/4

እንዲህን ነው ያመለጠችው ነፍሴ/2
እንደወፍ አመለጠች ነፍሴ /2
በረረች አመለጠች ነፍሴ /2
በአዳኝዋ በኢየሱሴ/4
በኢየሱሴ