From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
እግዚአብሔር ባይራራልኝ
ልጁን ልኮ ባይታደገኝ
የጠላት ሴራ ወጥመድ ዘርግቶብኝ
በሙታን ሰፈር እዛው ላይ በቀረሁኝ
ግን አልተሳካም አልሆነለትም
ነፍሴ ከቶ አላገኛትም
በክርስቶስ በተሰራው ስራ
አመለጠች እንደወፍ በራ
አመለጠች/4
ነፍሴ እንደወፍ ከአዳኞች ወጥመድ አመለጠች
በርራ በርራ እንደ ወፍ በርራ /2
አመለጠች በርራ /2
በክርስቶስ ስራ
አመለጠች በርራ
በመስቀል ላይ ስራ
አመለጠች በርራ
አዳኙ በስውር ወጥመድ አስቀመጠ
ከአሁን አሁን ያዘልኝ ሲል አይኑ እንዳፈጠጠ
አዳኜ ሲመጣ ወጥመዱን ሲረግጠው
ነፍሴን አስመልጦ ቀንበሩን ሰባበረው /4
እንዲህን ነው ያመለጠችው ነፍሴ/2
እንደወፍ አመለጠች ነፍሴ /2
በረረች አመለጠች ነፍሴ /2
በአዳኝዋ በኢየሱሴ/4
በኢየሱሴ
ሞትና ሲኦል አንድ ላይ ተስማምተው
ዘላለሜን ሊያደርጉት በድቅድቅ ጨለማው
የትንሳኤው ጉልበት ሞትን ራሱን ገድሎት
መውጊያውን ሰባብሮ ነፍሴ አስመለጣት/4
እንዲህን ነው ያመለጠችው ነፍሴ/2
እንደወፍ አመለጠች ነፍሴ /2
በረረች አመለጠች ነፍሴ /2
በአዳኝዋ በኢየሱሴ/4
በኢየሱሴ
|