ያረፈበት ፡ ዓይኔ (Yarefebet Aynie) - ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል
(Samuel Tesfamichael)

Samuel Tesfamichael 2.jpg


(2)

ግርማ ፡ ሞገስህ
(Germa Mogeseh)

ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 4:29
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Tesfamichael)

እንዲህ ፡ የምሆነው ፡ በዚህ ፡ ጉብዝናዬ

ያረፈበት ፡ ዓይኔ ፡ የወደደው ፡ ልቤ
በኢየሱስ ፡ ቁንጅና ፡ ላይ ፡ ነው ፡ ያለው ፡ ሀሳቤ
ያረፈበት ፡ ዓይኔ ፡ የወደደው ፡ ቀልቤ
በኢየሱስ ፡ ቁንጅና ፡ ላይ ፡ ነው ፡ ያለው ፡ ሃሳቤ

ፍጥረት ፡ በሙሉ ፡ ይየው ፡ ይየው ፡ ጌታን ፡ ይየው
አንዴ ፡ ቀምሶ ፡ ካጣጣመው ፡ ሌላ ፡ አያሰኘው

ሌላውን ፡ ላልወድ ፡ ሌላዉን ፡ ላልሻ
በሌላ ፡ ላልታለል ፡ ሌላዉን ፡ ላልሻ
ተማርኬያለሁ ፡ እስከመጨረሻ (፪x)
አመልከዋለሁ ፡ እስከመጨረሻ (፪x)

ያገር ፡ ቆንጆ ፡ ነኝ ፡ ባዩ ፡ ከውዴ ፡ ሲተያዩ
ያመረ ፡ መሳይ ፡ ዉበቱ ፡ ዉዴ ፡ ይበልጠዋል ፡ በስንቱ
ያገር ፡ ቆንጆ ፡ ነኝ ፡ ባዩ ፡ ከየሱስ ፡ ሲተያዩ
ያመረ ፡ መሳይ ፡ ዉበት ፡ ዉዴ ፡ በዛበት ፡ በስንቱ

ፍጥረት ፡ በሙሉ ፡ ይየዉ ፡ ይየው ፡ ጌታን ፡ ይየዉ
አንዴ ፡ ቀምሶ ፡ ካጣጣመዉ ፡ ሌላ ፡ አያሰኘዉ

እንዲህ ፡ የምሆነው (፪x)
የኢየሱስ ፡ ውበቱ ፡ ከሁሉ ፡ በልጦብኝ ፡ ነው
በዚህ ፡ ጉብዝናዬ ፡ ለዓለም ፡ ማልገዛው
ያዘጋጀው ፡ ክብር ፡ ከዓለም ፡ በልጦብኝ ፡ ነው (፪x)

አገር ፡ ሁሉ ፡ ያደነቀው ፡ ሰዓሊው ፡ የሳለው
አይ ፡ ሞኙ ፡ መች ፡ ገባው ፡ የኔን ፡ ቆንጆን ፡ አላየው
አገር ፡ ሁሉ ፡ ያደነቀው ፡ ሰዓሊው ፡ የሳለው
አይ ፡ ሞኙ ፡ መች ፡ ገባው ፡ ኢየሱሴን ፡ አላየው

ፍጥረት ፡ በሙሉ ፡ ይየዉ ፡ ይየው ፡ ጌታን ፡ ይየዉ
አንዴ ፡ ቀምሶ ፡ ካጣጣመዉ ፡ ሌላ ፡ አያሰኘዉ

ውበትን ፡ ላልፈልግ ፡ ዓለምን ፡ ላልሻ
በዓለም ፡ ላልታለል ፡ ውበትን ፡ ላልሻ
አግኘቸዋለሁ ፡ እስከመጨረሻ (፪x)
ወርሼዋለሁ ፡ እስከመጨረሻ (፪x)

እንዲህ ፡ የምሆነው (፪x)
የኢየሱስ ፡ ውበቱ ፡ ከሁሉ ፡ በልጦብኝ ፡ ነው
በዚህ ፡ ጉብዝናዬ ፡ ለዓለም ፡ ማልገዛው
ያዘጋጀው ፡ ክብር ፡ ከዓለም ፡ በልጦብኝ ፡ ነው (፬x)