ከጉባዔው ፡ መሃል (Kegubaew Mehal) - ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል
(Samuel Tesfamichael)

Samuel Tesfamichael 2.jpg


(2)

ግርማ ፡ ሞገስህ
(Germa Mogeseh)

ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 6:41
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Tesfamichael)

ከጉባዔው ፡ መሃል ፡ ብዙ ፡ ሕዝብም ፡ ካለበት
ተጋባዥ ፡ ሰው ፡ ሆኜ ፡ ያኔ ፡ በፍርሃት
ህዝቡ ፡ ብዙ ፡ ግን ፡ ባንድ ፡ ድምፅ ፡ አቤት ፡ ዝማርያቸው
መፅሐፍ ፡ ተከፍቶ ፡ ይነገራል ፡ ሰምቼ ፡ ማላውቀው (፪x)

ከቃሉ ፡ የህይወት ፡ ውሃ ፡ ወደልቤ ፡ ፈሰሰ
ሳላቅማማ ፡ ጠጣሁት ፡ ውስጤም ፡ ረሰረስ
ኧረ ፡ እንዴት ፡ ያለ ፡ ቀን ፡ ነው ፡ ዳግመኛ ፡ ተወለድኩኝ
በልቤ ፡ አምኝ ፡ በአፌም ፡ መሰከርኩኝ

በዚያን ፡ ቀን ፡ አሃሃ ፡ ታሪኬ ፡ ተቀየረ
በዚያን ፡ ቀን ፡ ኦሆሆ ፡ ቀንበሬ ፡ ተሰበረ
በዚያን ፡ ቀን ፡ ሽክሜም ፡ ቀለለልኝ
በዚያን ፡ ቀን ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ አልኩኝ

እንዳንተ ፡ ያለ ፡ ጌታ
አንተን ፡ መሳይ ፡ ወዳጅ
እንዳንተ ፡ ያለ ፡ መሃሪ
አንተን ፡ መሳይ ፡ አምላክ

ለማወቅ ፡ ተከፈቱ ፡ ዓይኖቼ
የመዳንን ፡ ቃል ፡ ሰምቼ
ወስኜ ፡ አንተን ፡ ያገኘሁባት
ያችን ፡ ቀን ፡ አልረሳት
ያችን ፡ ቀን ፡ ልባርካት (፪x)

ውዴ ፡ ደጁን ፡ ሲያንኳኳ ፡ በሬን ፡ ከፈትኩለት
ከእኔ ፡ ጋር ፡ እራት ፡ በላ ፡ የዋህ ፡ ነው ፡ በልቡ ፡ ትሁት
ተቆረሰ ፡ የሕይወት ፡ እንጀራ ፡ ዓይኖቼም ፡ ተከፈቱ
እንደንቦሳ ፡ ዘለልኩኝ ፡ አይረሳኝም ፡ ዕለቱ

በዚያን ፡ ቀን ፡ አሃሃ ፡ ኃጢያቴ ፡ ተሰረየ
በዚያን ፡ ቀን ፡ ኦሆሆ ፡ በሰማይ ፡ ደስታ ፡ ሆነ
በዚያን ፡ ቀን ፡ በአብ ፡ ቀኝ ፡ ተቀመጥኩኝ
በዚያን ፡ ቀን ፡ አምላክን ፡ እኔ ፡ ወረስኩኝ

እንዳንተ ፡ ያለ ፡ ጌታ
አንተን ፡ መሳይ ፡ ወዳጅ
እንዳንተ ፡ ያለ ፡ መሃሪ
አንተን ፡ መሳይ ፡ አምላክ

ለማወቅ ፡ ተከፈቱ ፡ ዓይኖቼ
የመዳንን ፡ ቃል ፡ ሰምቼ
ወስኜ ፡ አንተን ፡ ያገኘሁባት
ያችን ፡ ቀን ፡ አልረሳት
ያችን ፡ ቀን ፡ ልባርካት (፪x)

ይገርማል ፡ እኔን ፡ መውደድህ ፡ ይገርማል
ይገርማል ፡ እኔን ፡ ማሰብህ ፡ ይገርማል (፪x)

ይገርማል ፡ እኔን ፡ መውደድህ
ይገርማል ፡ እኔን ፡ ማሰብህ
ይገርማል ፡ እኔን ፡ ማፍቀርህ ፡ ይገርማል (፫x)