መቃብሩን ፡ ፈነቃቀለው (Meqaberun Feneqaqelew) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 7.jpg


(7)

የታመንኩትን ፡ አውቃለሁ
(Yetamenkuten Awqalehu)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 6:05
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

አዝመቃብሩን ፡ ፈነቃቀለው (፪x)
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ (፪x)

መቃብር ፡ ሊያዘው ፡ አልቻለም
ጌታችን ፡ ተቀብሮ ፡ አልቀረም
ጐልጐታ ፡ ላይ ፡ ሞቶ ፡ የነበረው
መቅብሩን ፡ ፈነቃቀለው
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ

አዝመቃብሩን ፡ ፈነቃቀለው (፪x)
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ (፪x)

ከሙታን ፡ መካከል ፡ ሕያውን
የምትፈልጉት ፡ አረ ፡ ለምን
እዚህ ፡ የለም ፡ ኢየሱስ ፡ ተነስቷል
መቃብሩን ፡ ባዶ ፡ አድርጐታል
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ

አዝመቃብሩን ፡ ፈነቃቀለው (፪x)
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ (፪x)

ወታደር ፡ ሲጠብቅ ፡ የቄሳር
ኢየሱስን ፡ ሊያስቀር ፡ መቃብር
ከኃይል ፡ ሁሉ ፡ በላይ ፡ ኃይል ፡ ያለው
መቃብሩን ፡ ፈነቃቀለው
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ

አዝመቃብሩን ፡ ፈነቃቀለው (፪x)
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ (፪x)
 
እንደ ፡ ሰው ፡ የሞተው ፡ ያ ፡ ጌታ
በድካሙ ፡ ጠላት ፡ የረታ
የሞትንም ፡ ጉልበት ፡ ሰባብሮ
ድል ፡ አድርጓል ፡ ማህተሙን ፡ ሽሮ
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ

አዝመቃብሩን ፡ ፈነቃቀለው (፪x)
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ (፪x)

መድኃኒት ፡ ከጽዮን ፡ የወጣ
ሊያድነን ፡ ከሰማይ ፡ የመጣ
ሞትን ፡ ለዘለዓለም ፡ የሻረው
መቃብሩን ፡ ፈነቃቀለው
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ

አዝመቃብሩን ፡ ፈነቃቀለው (፪x)
ተነሳ (፫x) ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ (፪x)