Ephrem Alemu/Acha Yelielew/Zemer Alegn

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ=ኤፍሬም ፡ ዓለ
ጠላት ፡ የጻፈው ፡ የሞት ፡ ደብዳቤ
ተቀዶ ፡ ሳየው ፡ ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ (ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ)
ጠላቴን ፡ ጥሎ ፡ ስላሳየኝ
ልቤም ፡ በደስታ ፡ ዘምር ፡ አለኝ (ዘምር ፡ አለኝ)

አዝ፦ ዘምር (፪x) (ዘምር ፡ አለኝ)
አምልክ (፪x) (አምልክ ፡ አለኝ)
ስገድ (፪x) (ስገድ ፡ አለኝ)
ለእርሱ ፡ ዘምር (ዘምር ፡ አለኝ)


ሸንጐ ፡ ሰብስቦብኝ ፡ መክሮብኛል ፡ ዝቶብኛል
ሰበብ ፡ ፈልጐብኝ ፡ ይዋጋኛል ፡ ይዞረኛል
የሚጠብቀኝ ፡ ስለማይተኛ ፡ እኔም ፡ አርፌ ፡ እስቲ ፡ ልተኛ
ዙሪያዬ ፡ ቢዞር ፡ ቢሽከረከረ ፡ እኔ ፡ እንደሆነ ፡ አለኝ ፡ ክብር
የተቀባ ፡ ሰው ፡ ሰልፉ ፡ ብዙ ፡ ነው
ነገር ፡ ግን ፡ ጌታ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ ነው

አዝ፦ ዘምር (፪x) (ዘምር ፡ አለኝ)
አምልክ (፪x) (አምልክ ፡ አለኝ)
ስገድ (፪x) (ስገድ ፡ አለኝ)
ለእርሱ ፡ ዘምር (ዘምር ፡ አለኝ)


የሲኦል ፡ በር ፡ ሲዘጋ ፡ ለእኔ ፡ ሌቱ ፡ ሲነጋ (ሲነጋ) ፡ ሲነጋ (ሲነጋ)
ጠላቴ ፡ ሲመሽበት ፡ ለማጁ ፡ ሰው ፡ በራለት ፡ ነጋለት (ነጋለት) ፡ በራለት (በራለት)
ደሙ ፡ ነው ፡ ምልክቴ ፡ አይገባም ፡ ሞት ፡ እቤቴ ፤ ከቤቴ (ከቤቴ) ፡ እቤቴ (ከቤቴ)
ያሳረገኝ ፡ ደሙ ፡ ነው ፡ ስለዚህ ፡ እዘምራለሁኝ ፡ ለጌታ (ለጌታ) ፡ በደስታ (በደስታ)

ምልክት ፡ አለብኝ ፡ የኢየሱስ ፡ ደም ፡ በግምባሬ
ይፈራኛል ፡ ጠላት ፡ ከቶ ፡ አይቀርብም ፡ በሰፈሬ
በአጠገቤ ፡ ሺ ፡ በቀኝ ፡ አስር ፡ ሺ ፡ እየጣለልኝ ፡ ሆንኩኝ ፡ ድል ፡ ነሺ
ዙሪያዬ ፡ ስሜ ፡ በደሙ ፡ ታጥሯል ፡ ቅዱስ ፡ መንፈሱ ፡ ይጠብቀኛል
በድል ፡ ወጥቼ ፡ በድል ፡ እገባለሁ ፡ የእኔ ፡ ከለላ ፡ የእሳት ፡ ቅጥር ፡ ነው

ጠላት ፡ የጻፈው ፡ የሞት ፡ ደብዳቤ
ተቀዶ ፡ ሳየው ፡ ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ (ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ)
ጠላቴን ፡ ጥሎ ፡ ስላሳየኝ
ልቤም ፡ በደስታ ፡ ዘምር ፡ አለኝ (ዘምር ፡ አለኝ)

አዝ፦ ዘምር (፪x) (ዘምር ፡ አለኝ)
አምልክ (፪x) (አምልክ ፡ አለኝ)
ስገድ (፪x) (ስገድ ፡ አለኝ)
ለእርሱ ፡ ዘምር (ዘምር ፡ አለኝ)


ምህረቱ ፡ በዝቶብኝ ፡ በሕይወቴ ፡ አለሁኝ
የእኔ ፡ ነው ፡ የምለው ፡ ምንም ፡ ነገር ፡ የሌለኝ
በቃ ፡ ማርኮኛል ፡ ተማርኬያለሁ ፡ ለፍቅሩ ፡ ብዛት ፡ እጄን ፡ ሰጥቻለሁ
ከአሁን ፡ በኋላ ፡ የምኖረው ፡ ለጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ልስሙ ፡ ነው
ዕድሜ ፡ ቀጥሎ ፡ ኑር ፡ ስላለኝ ፡ እኔም ፡ ለስሙ ፡ እኖራለሁኝ

ኦሮምኛ (ኦሮምኛውን ፡ ግጥም ፡ ይጻፉልን)
</poem> }}