Browse wiki

ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ርዕስ (Title) - ኤፍሬም ፡ ዓለ ጠላት ፡ የጻፈው ፡ የሞት ፡ ደብዳቤ ተቀዶ ፡ ሳየው ፡ ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ (ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ) ጠላቴን ፡ ጥሎ ፡ ስላሳየኝ ልቤም ፡ በደስታ ፡ ዘምር ፡ አለኝ (ዘምር ፡ አለኝ) :አዝ፦ ዘምር (፪x) (ዘምር ፡ አለኝ) ::አምልክ (፪x) (አምልክ ፡ አለኝ) ::ስገድ (፪x) (ስገድ ፡ አለኝ) ::ለእርሱ ፡ ዘምር (ዘምር ፡ አለኝ) ሸንጐ ፡ ሰብስቦብኝ ፡ መክሮብኛል ፡ ዝቶብኛል ሰበብ ፡ ፈልጐብኝ ፡ ይዋጋኛል ፡ ይዞረኛል የሚጠብቀኝ ፡ ስለማይተኛ ፡ እኔም ፡ አርፌ ፡ እስቲ ፡ ልተኛ ዙሪያዬ ፡ ቢዞር ፡ ቢሽከረከረ ፡ እኔ ፡ እንደሆነ ፡ አለኝ ፡ ክብር የተቀባ ፡ ሰው ፡ ሰልፉ ፡ ብዙ ፡ ነው ነገር ፡ ግን ፡ ጌታ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ ነው :አዝ፦ ዘምር (፪x) (ዘምር ፡ አለኝ) ::አምልክ (፪x) (አምልክ ፡ አለኝ) ::ስገድ (፪x) (ስገድ ፡ አለኝ) ::ለእርሱ ፡ ዘምር (ዘምር ፡ አለኝ) የሲኦል ፡ በር ፡ ሲዘጋ ፡ ለእኔ ፡ ሌቱ ፡ ሲነጋ (ሲነጋ) ፡ ሲነጋ (ሲነጋ) ጠላቴ ፡ ሲመሽበት ፡ ለማጁ ፡ ሰው ፡ በራለት ፡ ነጋለት (ነጋለት) ፡ በራለት (በራለት) ደሙ ፡ ነው ፡ ምልክቴ ፡ አይገባም ፡ ሞት ፡ እቤቴ ፤ ከቤቴ (ከቤቴ) ፡ እቤቴ (ከቤቴ) ያሳረገኝ ፡ ደሙ ፡ ነው ፡ ስለዚህ ፡ እዘምራለሁኝ ፡ ለጌታ (ለጌታ) ፡ በደስታ (በደስታ) ምልክት ፡ አለብኝ ፡ የኢየሱስ ፡ ደም ፡ በግምባሬ ይፈራኛል ፡ ጠላት ፡ ከቶ ፡ አይቀርብም ፡ በሰፈሬ በአጠገቤ ፡ ሺ ፡ በቀኝ ፡ አስር ፡ ሺ ፡ እየጣለልኝ ፡ ሆንኩኝ ፡ ድል ፡ ነሺ ዙሪያዬ ፡ ስሜ ፡ በደሙ ፡ ታጥሯል ፡ ቅዱስ ፡ መንፈሱ ፡ ይጠብቀኛል በድል ፡ ወጥቼ ፡ በድል ፡ እገባለሁ ፡ የእኔ ፡ ከለላ ፡ የእሳት ፡ ቅጥር ፡ ነው ጠላት ፡ የጻፈው ፡ የሞት ፡ ደብዳቤ ተቀዶ ፡ ሳየው ፡ ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ (ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ) ጠላቴን ፡ ጥሎ ፡ ስላሳየኝ ልቤም ፡ በደስታ ፡ ዘምር ፡ አለኝ (ዘምር ፡ አለኝ) :አዝ፦ ዘምር (፪x) (ዘምር ፡ አለኝ) ::አምልክ (፪x) (አምልክ ፡ አለኝ) ::ስገድ (፪x) (ስገድ ፡ አለኝ) ::ለእርሱ ፡ ዘምር (ዘምር ፡ አለኝ) ምህረቱ ፡ በዝቶብኝ ፡ በሕይወቴ ፡ አለሁኝ የእኔ ፡ ነው ፡ የምለው ፡ ምንም ፡ ነገር ፡ የሌለኝ በቃ ፡ ማርኮኛል ፡ ተማርኬያለሁ ፡ ለፍቅሩ ፡ ብዛት ፡ እጄን ፡ ሰጥቻለሁ ከአሁን ፡ በኋላ ፡ የምኖረው ፡ ለጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ልስሙ ፡ ነው ዕድሜ ፡ ቀጥሎ ፡ ኑር ፡ ስላለኝ ፡ እኔም ፡ ለስሙ ፡ እኖራለሁኝ ኦሮምኛ (ኦሮምኛውን ፡ ግጥም ፡ ይጻፉልን)
Information is currently being retrieved from the backend.