ያው ፡ ነው (Yaw New) - እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ
(Endale Woldegiorgis)

Endale Woldegiorgis 5.jpg


(5)

ዘላለማዊ
(Zelalemawi)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 4:43
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ ፡ አልበሞች
(Albums by Endale Woldegiorgis)

ዛሬ ፡ ብዬ ፡ የጠራሁት ፡ ቀን ፡ ትላንት ፡ ተብሎ ፡ አልፎ ፡ ሲወራ
ብርቱ ፡ መስሎ ፡ የታየው ፡ ሰው ፡ ለቀብሩ ፡ ሞቱ ፡ ሲሰማ
ፍጥረት ፡ ቦታውን ፡ ለቆ
የቆመው ፡ ደግሞ ፡ ወድቆ
ቀና ፡ ስል ፡ ኢየሱስ ፡ ያው ፡ ነው
ቀና ፡ ስል ፡ ጌታዬ ፡ ያው ፡ ነው ፡ ነው

ይባላ ፡ ቀና ፡ ይባላ ፡ ቀና
ብርቱ ፡ የሆነ ፡ አምላክ ፡ አለና
ይታይ ፡ ወደ ፡ ላይ ፡ ይታይ ፡ ወደ ፡ ላይ
ዘላለም ፡ ሚኖር ፡ አለ ፡ በሰማይ

አለሁ ፡ አለሁ ፡ ያለው ፡ ሰው
ድንገት ፡ ጉልበት ፡ ሲከዳው
ሁሉን ፡ ዘመን ፡ በቃ ፡ ሲለው
እንደ ፡ ጥላ ፡ ሲያሳልፈው
ንጉሠ ፡ ነገሥት ፡ ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ ዛሬም ፡ ያው
ግርማዊነቱ ፡ ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ ነገም ፡ ያው

ይባላ ፡ ቀና ፡ ይባላ ፡ ቀና
ብርቱ ፡ የሆነ ፡ አምላክ ፡ አለና
ይታይ ፡ ወደ ፡ ላይ ፡ ይታይ ፡ ወደ ፡ ላይ
ዘላለም ፡ ሚኖር ፡ አለ ፡ በሰማይ

አደራ ፡ የተባለው ፡ ለአደራው ፡ ሳይበቃ
ዓይን ፡ የተጣለበት ፡ ከስፍራው ፡ ሲታጣ
ማነው ፡ ጽኑ ፡ ብዬ ፡ ስጠይቅ ፡ ጥያቄ
ቃሉ ፡ እንዲህ ፡ እያለ ፡ ፈሰሰ ፡ ከውስጤ ፡

ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ትላንትናም ፡ ዛሬም ፡ እስከ ፡ ለዘላለም ፡ ያው ፡ ነው

አንቱ ፡ ተብሎ ፡ ሚወራለት
ጐንበስ ፡ ቀና ፡ ሚባልለት
እንዲያው ፡ ሲቀር ፡ በትዝታ
አንደ ፡ እለ ፡ ግን ፡ ሕያው ፡ ጌታ ፡
ንጉሠ ፡ ነገሥት ፡ ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ ዛሬም ፡ ያው
ግርማዊነቱ ፡ ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ ነገም ፡ ያው

ይባላ ፡ ቀና ፡ ይባላ ፡ ቀና
ብርቱ ፡ የሆነ ፡ አምላክ ፡ አለና
ይታይ ፡ ወደ ፡ ላይ ፡ ይታይ ፡ ወደ ፡ ላይ
ዘላለም ፡ ሚኖር ፡ አለ ፡ በሰማይ