ሙላኝ ፡ ተቆጣጠረኝ (Mulagn Teqotateregn) - እንዳለ ወልደጊዮርጊስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳለ ወልደጊዮርጊስ
(Endale Woldegiorgis)

Endale Woldegiorgis 5.jpg


(5)

ዘላለማዊ
(Zelalemawi)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 6:32
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳለ ወልደጊዮርጊስ ፡ አልበሞች
(Albums by Endale Woldegiorgis)

ጠልቄ ፡ መሄድ ፡ እፈልጋለሁ
የእኔ ፡ እርካታ ፡ የአንተ ፡ ክብር ፡ ነው
ላይ ፡ ላዩን ፡ መሄድ ፡ ይቅርብኝና
ይስጠም ፡ ሕይወቴ ፡ በህልውና (፪x)

መንፈስ ፡ ቅዱስ (፪x)

አዝ፦ ሙላኝ ፡ ተቆጣጠረኝ
ሌላ ፡ ሕይወት ፡ አይኑረኝ (፬x)

ላንብብ ፡ ቃልህን ፡ ልስማ ሕግህን
ላድርግ ፡ ስራዬን ፡ ደስ ፡ የሚልህን
መቅደስነቴ ፡ ለአንተ ፡ ብቻ ፡ ነው
የለኝም ፡ በአንተ ፡ ላይ ፡ ደባል ፡ የማደርገው
ከምር ፡ ነው ፡ ከልብ ነው
የአንተ መሆን ምፈልገው
ማንከስ ፡ ይቅር ፡ በሃሳቤ
ልከተልህ ፡ ቆርጦ ፡ ልቤ

አዝ፦ ሙላኝ ፡ ተቆጣጠረኝ
ሌላ ፡ ሕይወት ፡ አይኑረኝ (፬x)

እኔ ፡ ግን ፡ እኔ ግን (፪x)
በጽድቅህ ፡ ፊትህን ፡ አያለሁ
ክብርህን ፡ ሳይ ፡ እጠግባለሁ (፪x)

ቁርጭምጭሚት ፡ ጋ ፡ ባለው ፡ ሕይወቴ
በቃኝ ፡ አልበል ፡ በዚህ ፡ ረክቼ
ጉልበቴን ፡ እና ፡ ወገቤን ፡ አልፈህ
ተቆጣጠረኝ ፡ ከሁሉ ፡ ልቀህ

በአንተ ፡ ተይዞ ፡ ሁሉ ፡ ነገሬ
ቢያልቅ ፡ ይሻላል ፡ ቀሪ ፡ ዘመኔ

ጠልቄ ፡ መሄድ ፡ እፈልጋለሁ
የእኔ ፡ እርካታ ፡ የአንተ ፡ ክብር ፡ ነው
ላይ ፡ ላዩን ፡ መሄድ ፡ ይቅርብኝና
ይስጠም ፡ ሕይወቴ ፡ በህልውናህ (፪x)

መንፈስ ፡ ቅዱስ (፪x)

አዝ፦ ሙላኝ ፡ ተቆጣጠረኝ
ሌላ ፡ ሕይወት ፡ አይኑረኝ (፬x)