ጉልበቴ (Gulbetie) - እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ
(Endale Woldegiorgis)

Endale Woldegiorgis 3.jpg


(3)

ይቤዠኛል
(Yebezegnal)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2009)
ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ ፡ አልበሞች
(Albums by Endale Woldegiorgis)

በግብፅ ፡ የነበረውን ፡ የህዝቡን ፡ ጩኸት ፡ የሰማ ፡ ጌታ
ጊዜና ፡ ዘመን ፡ ጠብቆ ፡ ወደኔ ፡ መጣ
በቃ ፡ አለው (፪x) ፡ ያን ፡ ክፉ
በቃ ፡ አለው ፡ ያን ፡ ክፉ
ጌታዬ ፡ ከልሎኝ ፡ በክንፉ (፬x)

ያቤቱታ ፡ ድምፄ ፡ ወደ ፡ ጆሮው ፡ ደርሶ
የምህረት ፡ ፊቱን ፡ ወደኔ ፡ መልሶ
ከጨቋኙ ፡ ገዢ ፡ ነፍሴን ፡ አላቋታል
ውስጤን ፡ በደስታ ፡ እንዲህ ፡ አስብሎታል ፡ አሄ

አስባለሁ ፡ እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማን ፡ አለ (፪x)
እላለሁ ፡ እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማን ፡ አለ (፪x)

በውርደቴ ፡ መንደር ፡ ክብር ፡ ያየሁበት
የቆሰለው ፡ ልቤ ፡ የተፈወሰበት (፪x)

እላለሁ ፡ እላለሁ ፡ እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ የለም ፡ አሜን (፪x)

እንደ ፡ ወትሮው ፡ ሰላም ፡ አውለኝ ፡ ብዬ ፡ ስነሳ
የፈሮኦንን ፡ ጡብ ፡ ልሰራለት ፡ ከቤት ፡ ስወጣ
ያስገባሪዬን ፡ ገመድ ፡ ከላዬ ፡ ሊፈታልኝ
አምላኬ ፡ መጣ ፡ ያዘንኩበትን ፡ ቀን ፡ ቀጥሮልኝ
ግብፅን ፡ ለቅቄ ፡ ያን ፡ ቀን ፡ ስወጣ
ፈርኦን ፡ ሲያየኝ ፡ እንዲህ ፡ አልኩታ

ጉልበቴ (፪x)
ላዳነኝ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ ጉልበቴ
አትበላው ፡ ከሳሼ

በግብፅ ፡ የነበረውን ፡ የህዝቡን ፡ ጩኸት ፡ የሰማ ፡ ጌታ
ጊዜና ፡ ዘመን ፡ ጠብቆ ፡ ወደኔ ፡ መጣ
በቃ ፡ አለው (፪x) ፡ ያን ፡ ክፉ
በቃ ፡ አለው ፡ ያን ፡ ክፉ
ጌታዬ ፡ ከልሎኝ ፡ በክንፉ (፬x)