ድሮ ፡ ገና (Dero Gena) - ዳዊት ፡ ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ፡ ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Dawit Getachew 1.jpg


(1)

እጠብቅሃለሁ
(Etebeqehalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2010)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 5:37
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ፡ ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ድሮ ፡ ገና ፡ ከማህፀን ፡ ሳለሁ ፡ በእናቴ ፡ ሆድ
በሥም ፡ ጠርተህ ፡ የለየኸኝ ፡ ክፉን ፡ ደጉን ፡ ሳላውቅ
የአንተ ፡ ክብር ፡ መገለጫ ፡ እንድሆን ፡ በቤትህ
ከነኃጢአቴ ፡ የመረጥከኝ ፡ ለአንተ ፡ እንድኖርልህ

በሰጠኸኝ ፡ መንገድ ፡ ስሄድ ፡ ባሰብክልኝ ፡ ስፍራ
እንዳልገኝ ፡ ሳሳዝንህ ፡ ቸል ፡ ብዬ ፡ ሳልሰማህ
ዛሬ ፡ በቀን ፡ ለምንሃለሁ ፡ ኃይልህ ፡ እንዲረዳኝ
በመክሊቴ ፡ ብዙ ፡ አትርፌ ፡ አንተን ፡ ደስ ፡ እንዳሰኝ

አዝ:- ኃይልህ ፡ ይርዳኝ ፡ ለምናለው
እንድትረዳኝም ፡ አምናለሁ
መልካም ፡ ነገር ፡ ያደረኩኝ ፡ መስሎኝ
ሳሳዝንህ ፡ እንዳልገኝ

ስመላለስ ፡ በዚህች ፡ ምድር ፡ ሳገለግል ፡ አንተን
የማልኖረውን ፡ አውርቼ ፡ የተጣልኩ ፡ እንዳልሆን
እንዳታልፈኝ ፡ እፈራለሁ ፡ በምትመጣበት ፡ ቀን
ሕይወቴም ፡ አንተን ፡ ያክብርህ ፡ አፌ ፡ ብቻ ፡ ሳይሆን

ክብርህን ፡ አሳየኝ ፡ የአንተን ፡ ማንነት
ቅዱሱን ፡ መንፈስህን ፡ ሚመራኝ ፡ ወደ ፡ እውነት
እኔ ፡ ደካማና ፡ ኃጢአተኛ ፡ ሰው ፡ ነኝ
ሃይልህ ፡ ግን ፡ ከረዳኝ ፡ ከእግሬ ፡ እቆማለሁ

አዝ:- ኃይልህ ፡ ይርዳኝ ፡ ለምናለው
እንድትረዳኝም ፡ አምናለሁ
መልካም ፡ ነገር ፡ ያደረኩኝ ፡ መስሎኝ
ሳሳዝንህ ፡ እንዳልገኝ

ቀድመህ ፡ ውጣ ፡ በሕይወቴ
ልከተልህ ፡ ቸሩ ፡ አባቴ
አንተ ፡ ቀድመኀኝ ፡ ካልወጣህ
እኔ ፡ ብሮጥ ፡ ምን ፡ ላመጣ

ለምንሃለሁ ፡ ጌታ
ለምንሃለሁ ፡ ኢየሱስ
ኃይልህ ፡ ይርዳኝ ፡ ጌታ