በምህረቱ (Bemeheretu) - ዳዊት ፡ ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ፡ ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Dawit Getachew 1.jpg


(1)

እጠብቅሃለሁ
(Etebeqehalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2010)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 5:25
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ፡ ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ኃጥያተኛ ፡ ነበርኩ ፡ ዓለም ፡ ጉድ ፡ ያለልኝ
ለሰራሁት ፡ በደል ፡ ሞት ፡ የፈረዱብኝ
ገበናዬን ፡ ገልጠው ፡ እየገፈተሩኝ
ለፍርድ ፡ አቀረቡኝ ፡ በድንጋይ ፡ ሊወግሩኝ

ዳኛው ፡ ግን ፡ ስለ ፡ እኔ ፡ በእውነት ፡ አዘነልኝ
ውስጡን ፡ እያወቀ ፡ ለእኔ ፡ ፈረደልኝ
ከከሳሾቼ ፡ እጅ ፡ በጥበብ ፡ አስጥሎኝ
በእኔ ፡ ፋንታ ፡ እርሱ ፡ ሞቶ ፡ ከፈለልኝ

አዝ:- በምህረቱ ፡ ዛሬ ፡ ቆሜያለሁ
ስለ ፡ እኔ ፡ ሞቶ ፡ እኔ ፡ ድኛለሁ
ነፍሴን ፡ ከሚሹ ፡ ከከሳሾቼ
ማምለጥ ፡ ችያለሁ ፡ ምህረት ፡ አግኝቼ

ስለ ፡ እኔ ፡ ሞቶ ፡ እኔ ፡ ድኛለሁ

የምህረቱ ፡ ብዛት ፡ ከባሕር ፡ ይጠልቃል
ስለኀጢያተኛው ፡ በእውነት ፡ ግድ ፡ ይለዋል
እርሱ ፡ ነው ፡ ዳኛዬ ፡ የሆነኝ ፡ ጠበቃ
ቀድሞ ፡ የታደገኝ ፡ ሕይወቴ ፡ ሲያበቃ

ከሳሾቼ ፡ ሁሉ ፡ ድንጋያቸውን ፡ ጥለው
ወደ ፡ ኋላ ፡ ሸሹ ፡ ህሊና ፡ ወቅሷቸው
ስራዬን ፡ ሰርቶታል ፡ አሁን ፡ ነጻ ፡ ሰው ፡ ነኝ
ላዳነኝ ፡ ኢየሱስ ፡ እዘምራለሁኝ

አዝ:- በምህረቱ ፡ ዛሬ ፡ ቆሜያለሁ
ስለ ፡ እኔ ፡ ሞቶ ፡ እኔ ፡ ድኛለሁ
ነፍሴን ፡ ከሚሹ ፡ ከከሳሾቼ
ማምለጥ ፡ ችያለሁ ፡ ምህረት ፡ አግኝቼ

ዋጋዬ ፡ ይሄ ፡ ነው
በእርሱ ፡ ደም ፡ ታጥቤያለሁ ፡ እኔ ፡ ድኛለሁ
ስለ ፡ እኔ ፡ ሞቶ ፡ አድኖኛል
በእርሱ ፡ ቁስል ፡ ተፌውሻለሁ

ነፍሴን ፡ ከሚሹ ፡ ከአዳኝ ፡ ወጥመድ
አስመለጠኝ ፡ አኔን ፡ አዳነኝ
ዛሬ ፡ በደስታ ፡ ዘምራለሁ
በእርሱ ፡ ቁስል ፡ እኔ ፡ ድኛለሁ

ፍቅሩን ፡ እያሰብኩ ፡ በፊቱ ፡ ዘምራለሁ
ከሞት ፡ አፍ ፡ ከጫፍ ፡ ላይ ፡ አውጥቶኛልና
ታሪኬን ፡ አወራለሁ
ምህረቱን ፡ እያሰብኩ ፡ በፊቱ ፡ ዘምራለሁ
ለነፍሴ ፡ መዳን ፡ ሆኖላታልና
ሥሙን ፡ እባርካለሁ (፪x)