የእየሱስ መንገድ (Ye Eyesus Menged) - ዳዊት ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Lyrics.jpg


(2)

አልበም
(Amnihalehu)

ቁጥር (Track):

፲ ፬ (14)

ርዝመት (Len.): 5:50
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

በዚህች ምድር ስኖር ብርቱ ሰልፍ ቢኖርም
ንፋስ ማዕበሉ ሊጥሉኝ ቢጥሩም
እምነቴን ሊፈትን ዙሪያዩን ቢዞርም
የጠራኝ ክርስቶስ ስለኔ አሸንፎአል ሁሉንም

እሮጣለሁ ይሄን የጽድቅ ጎዳና
እሮጣለሁ ይሄን የህይወት መንገድ
ወስኛለው መስቀሉን እያየሁ ልሄድ
ከኢየሱስ ሌላ ላልወድ
ወደ ኋላም ከቶ ላልሄድ

ግብ ግብ ከኔ ጋር ብዙ ቢያዝለኝም
ነፍስን በሚያደክም ትግል ውስጥ ብኖርም
ስጋዩን እየጎሸምኩ ወደ ፊት እሔዳለሁ
የምኖርለትን አላማ እያየሁ

እሮጣለሁ ይሄን የጽድቅ ጎዳና
እሮጣለሁ ይሄን የህይወት መንገድ
ወስኛለው መስቀሉን እያየሁ ልሄድ
ከኢየሱስ ሌላ ላልወድ
ወደ ኋላም ከቶ ላልሄድ

በፀጋው ጉልበት እታመናለሁ
ብወድቅም እንኳን ዳግም እቆማለሁ
ግን እስከ ፍፃሜ መስቀሉን እያየሁ
የኢየሱስን መንገድ እኖረዋለሁ

ኢየሱስን ነው አይኔ የሚያየው
ኢየሱስን ነው ተስፋ የማደርገው
መስቀሉን ብቻ ነው ትኩር ብዩ የማየው
እስከፍጻሜ ለክብር እሮጣለሁ