ፀጋው በእምነት አድኖናል (Tsegaw Bemnet Adinonal) - ዳዊት ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Lyrics.jpg


(2)

አምንሃለሁ
(Aminhalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ ፬ (2021)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 5:10
ጸሐፊ (Writer): ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew
Property "Writer" has been marked for restricted use.
)
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ሰዉን : ሁሉ : የሚያድን : የእግዚአብሄር : ፀጋ : በክርስቶስ : በኩል : ተገልጧል
ለሚያምን : ሁሉ : የኃጢያት : ስርየት : እንዲሁ : በነፃ : ያደርጋል
ተስፋ : ለቆረጡ : ለተጨነቁ  : በሞት : ጥላ : ውስጥ : ላሉ :ሁሉ
ወደ : ህይወት : መንገድ : ይመራቸዋል : ጉልበት : አለው : ደሙ

   አዝ:- ፀጋው : በእምነት : አድኖናል
        ክርስቶስ : ቤዛ : ሆኖልናል
        ይህም : የእግዚአብሄር : ስጦታ : እንጂ
        ከእኛ : ስላይደለ : ከቶ : እንደለፋንበት : አንመካም

ቅን : ፈራጅ : ጻድቅ : አምላክ : ነው : እና : እንከን : የሌለበት
ኃጢያተኛውን : ሊያጸድቅ : ወዶ : ልጁን : አደረገው : ኃጢያት
እዉነትን : እና : ምህረትን : አስማምቶ : እኛን  :አፀደቀን
በክርስቶስ : በኩል : በነፃ : የተሰጠን : የፀጋው : ክብር : ይመስገን

   አዝ:- ፀጋው : በእምነት : አድኖናል
        ክርስቶስ : ቤዛ : ሆኖልናል
        ይህም : የእግዚአብሄር : ስጦታ : እንጂ
        ከእኛ : ስላይደለ : ከቶ : እንደለፋንበት : አንመካም

ስለሚገባን : ሳይሆን : እንዲው : ስለወደደን
ከዘላለም : ሞት : ሊያድነን : ፀጋውን : ላከልን
እያስተማረ : እየረዳ : እስከፍጻሜው : ሊያደርሰን
እግዚአብሄርን : እንድንመስል : ፀጋው : ነው : የሚረዳን

በፀጋው : ክብር : ይሁን
ላዳነን : ክብር : ይሁን
ለኢየሱስ : ክብር : ይሁን
ይገባዋል : እና : ክብር : እና : ምስጋና : አሜን

በፀጋው : ክብር : ይሁን
ላዳነን : ክብር : ይሁን
ለኢየሱስ : ክብር : ይሁን
አድኖናል : እና : እንዲሁ : በፀጋ : አሜን