ትልቅ ነህ (Tilik Neh) - ዳዊት ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Lyrics.jpg


(2)

አልበም
(Amnihalehu)

ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 5:13
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ደማቁ ብርሃን በአንተ ይሰወራል
ህያው ማንነትህ ከዘላለም ያልፋል
አቤት የአንተ ውበት ሞገስህ ሲያበራ
አትወዳደርም ከሰራኸው ጋራ

ትልቅ ነህ ከምንልህ በላይ
ከገባህን በላይ ከሰበክንህ በላይ
ኀያል ነህ ብለን ካልንህ በላይ
ከዘመርንህ በላይ እግዚአብሔር ሆይ

ለግዛትህ ወሰን ፋፃሜ የለውም
በእጅህ ላይ ናቸው ዛሬና ዘላለም
ከጊዜ ውጭ ያለህ በጊዜ ምትሰራ
ዙፋንህ የፀና የለ የሚያስፈራህ

ትልቅ ነህ ከምንልህ በላይ
ከገባህን በላይ ከሰበክንህ በላይ
ኀያል ነህ ብለን ካልንህ በላይ
ከዘመርንህ በላይ እግዚአብሔር ሆይ

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ያለና የነበርክ
ለዘላለም የምትኖር በግርማህ
ሰማይና ምድር በክብርህ ተሞልቷል
እግዚአብሔር አንተን ከቶ ማን ይመስላል

አንተ ልዩ ነህ አንተ ልዩ ነህ
ልዩ ነህ አንተ ልዩ ነህ

ትልቅ ነህ ከምንልህ በላይ
ከገባህን በላይ ከሰበክንህ በላይ
ኀያል ነህ ብለን ካልንህ በላይ
ከዘመርንህ በላይ እግዚአብሔር ሆይ