ስምህን እባርካለሁ (Semehin Ebarikalew) - ዳዊት ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Lyrics.jpg


(2)

አልበም
(Aminhalehu)

ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 5:49
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ሁሉን የምትችል የዘላለም ንጉስ እግዚአብሔር
ያለህ የነበርህ ወደፊትም የምትኖር
ታላቅነት ሞገስ የሚገባህ ምስጋና ክብር
ኀይል ጥበብ ብርታት መንግሥት የአንተ ነው በሰማይ በምድር

ስምህን እንባርካለን ስምህን እንባርካለን
እግዚአብሔር አዳኝነትህን ዘውትር እንወድሳለን

በቅዱሱ ክንድህ አስመልጠኸናል
በድንቅ በተአምራት ማዳንህን አይተናል
ፀጋህ ባያግዘን ፍቅርህ ባይዘን
ምህረትህ ደግፎ እዚህ ባያደርሰን

በጠፋን ነበረ አንተ ባትደርስልን
ግን ምህረት ቸርነትህ በቤትህ አኖረን
በጠፋን ነበረ አንተ ባትደርስልን
ግን ምህረት ቸርነትህ በህይወት አኖረን

ሁሉ ከአንተ በአንተ ለአንተ ነው እኛ ምን አለን
የተቀበልነውን ከደጉ እጅህ እንሰጥሃለን
ስለቸርነትህ ስላረክልን ምን እንከፍላለን
እግዚአብሔር ሆይ ስምህን ለዘላለም እንባርካለን

ስምህን እንባርካለን ስምህን እንባርካለን
እግዚአብሔር አዳኝነትህን ዘውትር እንወድሳለን

ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን
በምህረት አምጥተህ ካህናት ያረከን
በኃያሉ ክንድህ አምልጠናልና
ዘውትር እንሰዋለን ለስምህ ምስጋና

በጠፋን ነበረ አንተ ባትደርስልን
ግን ምህረት ቸርነትህ በቤትህ አቆመን
በጠፋን ነበረ አንተ ባትደርስልን
ግን ምህረት ቸርነትህ በህይወት አኖረን