በቂ ነህ (Beki Neh) - ዳዊት ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Lyrics.jpg


(2)

አልበም
(Aminhalehu)

ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 4:30
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ምን ቀረኝ ከእንግዲህ ሁሉን ሰጠኸኝ
የመንግሥትህ ወራሽ በልጅህ ሆንኩኝ
ከአንተ የተነሳ ተስፋዬ ሙሉ ነው
በሚያስጨንቅ ዘመን ቆሜ ስቃለው

አንተን እንጂ ሁኔታን ከቶ አላይም
በእምነት እንጂ በሚታየው አልሄድም
እረፍትና ሰላም የመንፈስም ደስታ
ፍለጋ አትሄድም ነፍሴ ከአንተ ወጥታ

ዝማሬዬ ነህ የልቤ ደስታ
ነፍሴ ረክታለች ውዷን አግኝታ
ከበቂም በላይ በአንተ አርፌያለሁ
እግዚአብሔር ሆይ እወድሃለው

በአንተ ሁልጊዜ ደስ ደስ ይለኛል
በአብሮነትህ ልቤ ይጓደዳል
እጅህ በሰራት በዚች ቀን ላይ ቆሜ
አመሰግናለሁ ስለ ሰላሜ

ሀብት ቢሞላ ቢትረፈረፍ ከንቱ ነው
ሰላምን ከምንጩ ጨልፎ አያመጣው
በሁሉ ሁልጊዜ ደስ የሚያሰኘኝ
የአንተ ሰላም ነው በክርስቶስ ያለኝ

ዝማሬዬ ነህ የልቤ ደስታ
ነፍሴ ረክታለች ውዷን አግኝታ
ከበቂም በላይ በአንተ አርፌያለሁ
እግዚአብሔር ሆይ እወድሃለው

የማያቋርጥ እረፍት የማይነጥፍ ደስታ
በማዕበል ውስጥ እረፍት በመናወጥ ፈንታ
ከጸጋህ የተነሳ ዝም ብዬ እስቃለሁ
ኑሮዬ ይበቃኛል ማለት ተምሬያለሁ

የማያቋርጥ እረፍት የማይነጥፍ ደስታ
በማዕበል ውስጥ እረፍት በመናወጥ ፈንታ
ከጸጋህ የተነሳ ዝም ብዬ እስቃለሁ
ኑሮዬ ይበቃኛል ማለት ተምሬያለሁ

የማያቋርጥ እረፍት (የማይነጥፍ ደስታ)
በማዕበል ውስጥ እረፍት በመናወጥ ፈንታ
ከጸጋህ የተነሳ ዝም ብዬ እስቃለሁ
ኑሮዬ ይበቃኛል ማለት ተምሬያለሁ