አፀደቀን (Atsedeken) - ዳዊት ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Lyrics.jpg


(2)

አምንሀለው
(amnihalehu)

ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 5:46
ጸሐፊ (Writer): ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew
Property "Writer" has been marked for restricted use.
)
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ክብር ፡ ምስጋና ፡ ይሁን ፡ ለእግዚአብሄር
ወዶናልና ፡ ከቶ ፡ ላይተወን ፡ በዘላለም ፡ ፍቅር
ክብር ፡ ምስጋና ፡ ይሁን ፡ ለእግዚአብሄር
በእራሱ ፡ ምሏል ፡ ከቶ ፡ ላይተወን ፡ ታላቅ ፡ እርስት ፡ ሆነን

ወድቀን ፡ ሳለን ፡ ተጥለን ፡ስንጨነቅ ፡ ሚረዳን ፡ አተን
በደም ፡ ተለዉሰን ፡ ሳለን ፡ በብዙ ፡ ስቃይ ፡ ተስፋ ፡ ቆርጠን
አይቶ ፡ እጅግ ፡ እራራልን ፡ ቁስላችንን ፡ አጥቦ ፡ ፈወሰን
ልጁን ፡ በወደደበት ፡ ፍቅር ፡ እኛንም ፡ እንዲሁ ፡ ወደደን

   አዝ፦ አዳነን ፡ ከጨለማ ፡ ወደሚደነቅ ፡ ብርሃኑም ፡ ጠራን
      የእርሱን ፡ ፍቅር ፡ በጎነት ፡ እንድንናገር ፡ ተመረጥን
      ታላቅ ፡ ህዝብ ፡ አደረገን ፡ የተለየን ፡ የንጉስ ፡ ካህን
      ምህረትን ፡ አግኝተን ፡ ተባልን ፡ የእግዚአብሄር ፡ ወገን

ወገን /3/ ወገን : አደረገን
ልጆች /3/ ልጆቹ : አረገን
አፀደቀን...

አምላክ ፡ ተብሎ ፡ ሊጠራብን ፡ እግዚአብሄር ፡ ስላላፈረብን
ከእርሱ ፡ ጋር ፡ አብረን ፡ እንድንኖር ፡ በሰማይ ፡ ስፍራ ፡ አዘጋጀልን
ወደደን ፡ ደግሞም ፡ አፀደቀን ፡ ከእንግዲ ፡ ማነው ፡ ሚኮንነን
ሰቶናል ፡ የልጅነት ፡ መንፈስ ፡ እንድንጠራው ፡ አብ ፡ አባት ፡ ብለን

   አዝ፦ አዳነን ፡ ከጨለማ ፡ ወደሚደነቅ ፡ ብርሃኑም ፡ ጠራን
      የእርሱን ፡ ፍቅር ፡ በጎነት ፡ እንድንናገር ፡ ተመረጥን
      ታላቅ ፡ ህዝብ ፡ አደረገን ፡ የተለየን ፡ የንጉስ ፡ ካህን
      ምህረትን ፡ አግኝተን ፡ ተባልን ፡ የእግዚአብሄር ፡ ወገን

ወገን /3/ ወገን : አደረገን
ልጆች /3/ ልጆቹ : አረገን
አፀደቀን...