አንተ ብቻ (Ante Bicha) - ዳዊት ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Lyrics.jpg


(2)

አልበም
(Amnihalehu)

ቁጥር (Track):

፲ ፭ (15)

ርዝመት (Len.): 5:10
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ከምድር ጫፍ እስከ ጫፍ
ለክብርህ አህዛብ ቢሰለፍ
አይበዛብህም ቢዘመርልህ
አያንስብህም ባንሰዋልህ

አንተ ያው እግዚአብሔር ነህ
የሚመስልህ የሌለህ
ለዘላለምም ጸንተሀል
ካንተ በላይስ ክብር የታል

አንተ ብቻ እግዚአብሔር
በዙፋንህ ጸንተህ የምትኖር
ታላቅ አምላክ ነህና
ክንድህ የጸና

ሁሉን በቃልህ ፈጠርክ
በእስትንፋስህ ምድርን ሞላህ
የሚመስልህ የሌለህ
ድንቅ አምላክ ነህ

ሐያላን የታሉ
አንተ ላይ የተማማሉ
ተረት ሆነ ታሪካቸው
እስትንፋስህ በተናቸው
አንተ ግን በክብርህ
እስካሁን እንዳማረብህ
ታላቅ ክንድህም አልደከመም
ታምር ይስራል ለዘለዓለም
አንተ ብቻ እግዚአብሔር
በዙፋንህ ጸንተህ የምትኖር
ሀያል አምላክ ነህና
ክንድህ የጸና
ሁሉን በቃልህ ፈጠርክ
በእስትንፋስህ ምድርን ሞላህ
የሚመስልህ የሌለህ
ድንቅ አምላክ ነህ

ከፍጥረት ጋራ አብሬ
አቀርባለሁ ዝማሬ
ባይመጥንህም እንኳን
ታላቅ ክብር
ዝም ከማለት ይልቅ
መጥቻለው ላደንቅህ
ታላቅነትህን እያየሁ
ዘምራለሁ

ሀያል ነህ ሀያል 2 x
እግዚአብሔር ሀያል ነህ
ክንድህ ሀያል ነው

ሀያል ነህ ሀያል 2 x
በቻህን ሀያል
ብርቱ ነህ ብርቱ 2 x
እግዚአብሔር ብርቱ ነህ

ብርቱ ነህ ብርቱ 4x
ሕያው ነህ ሕያው 2 x
እግዚአብሔር ሕያው ነህ
ሕያው ነህ ሕያው 2 x
ያለህ የነበርክ ሕያው

ደግሞም የምትነግስ ንጉስ
ንጉስ ነህ ንጉስ ነህ 3 x