አመልክሃለው (Amelkihalehu) - ዳዊት ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Lyrics.jpg


(2)

አልበም
(Amnihalehu)

ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 5:24
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

አንተ ከቶ የማታውቀው በሂወቴ ምን አለ
ገና ሳልነግርህ ይገባህ የለ የልቤ እንዳለ
ስለዚህ ጥያቄዬን ገትቼ ላምልክህ ላክብርህ
ነውና የዘውትር ስራዬ መቀደስ ስምህን

እንዲህ እንዲያ እያልኩ ጊዜዬን አልፈጅም
አንተን ከፍ ሳደርግ ያንስብኛል ሁሉም
የመኖሬ አላማ ለአንተ ክብር ነው
ዘላለም ማምለኬን ሁኔታ አይቀይረው

ጌታ ከቶ የማታውቀው በሂወቴ ምን አለ
ገና ሳልነግርህ ይገባህ የለ የልቤ እንዳለ
ስለዚህ ጥያቄዬን ገትቼ ላምልክህ ላክብርህ
ነውና የዘውትር ስራዬ መወደስ ስምህን

አንተ እኮ ትልቅ ነህ ከነገሮች በላይ
ከአፍህ በወጣው ቃል ፍጥረት ፀንቶ የለም ወይ
ሁኔታ ያልቃኘው አምልኮና ክብር
እሰዋለው ዘውትር ላንተ ለእግዚአብሔር

እጆቼን ከፍ አድርጌ ስምህን እባርካለው
የሚገባህን ሁሉ ይዤ በፊትህ እቀርባለው
በእውነትና በመንፈስ
ነፍሴን በፊትህ ላፍስስ
ደስ ያሰኝህ መስዋቴ
ይሄ ነው የልብ መሻቴ

እግዚአብሔርነትህን አመልካለሁ
ክብርህን እያየሁ አመልካለሁ
ከሁኔታ በላይ አመልካለሁ
ፊትህን እያየሁ አመልካለሁ