ትበቃኛለህ (Tebeqagnaleh) - ቤተልሔም ፡ ወልዴ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ወልዴ
(Bethlehem Wolde)

Bethlehem Wolde 3.png


(3)

ቃልህን ፡ ወደድኩት
(Qalehen Wededkut)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2007)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 5:07
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ወልዴ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Wolde)

ከሆነልኝ ፡ ነገር ፡ ሁሉ ፡ ይልቅ
ያረከው ፡ አንተ ፡ ሆንክልኝ ፡ ድንቅ (፪x)

ስለዚህ ፡ ትበቃኛለህ
ሁልጊዜ ፡ ታስመካኛለህ (፪x)

የከበደኝን ፡ ሁሉ ፡ አንተ ፡ አቀለልከው
ፀሎቴንም ፡ እየሰማህ ፡ ጥያቄዬን ፡ መለስከው
ለሰው ፡ ልጆች ፡ መልካምን ፡ በማድረግ ፡ ደስ ፡ ይልሃል
ልዩ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ማንስ ፡ ይመስልሃል

ስለዚህ ፡ ትበቃኛለህ
ሁልጊዜ ፡ ታስመካኛለህ (፪x)

በዕድሌ ፡ እኮ ፡ አይደለም ፡ በደረሰኝ ፡ እጣ
ምታኖረኝ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ ፡ ሁሌ ፡ ባለጠጋ
በክንዶችህ ፡ ተማምኜ ፡ በጥላህ ፡ አድራለሁ
ጥጋቤ ፡ ነህ ፡ እርካታዬ ፡ አርፌብሃለሁ

አዝ፦ ስለዚህ ፡ ትበቃኛለህ
ሁልጊዜ ፡ ታስመካኛለህ (፪x)

በልቤ ፡ ውስጥ ፡ ያለው ፡ ሞልቶ ፡ የፈሰሰው (፪x)
በውስጤ ፡ ያረከው ፡ የፍቅር ፡ እሳት ፡ ነው (፪x)
ይህንን ፡ አይቼ ፡ እንዴት ፡ ዝም ፡ እላለሁ (፪x)
በአዲስ ፡ በአዲስ ፡ ዜማ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)

የእኔ ፡ ጌታ ፡ ተባረክልኝ (፫x)
ሌላማ ፡ ምን ፡ እልሃለሁ ፡ ተባረክልኝ (፪x)

ሰልፉን ፡ ለአንተ ፡ ሰጠሁ ፡ እኔ ፡ እቆማለሁ (፪x)
ቸርነት ፡ ምህረትህን ፡ ሁሌ ፡ እናገራለሁ (፪x)
ድብቅ ፡ ጦር ፡ አንስተህ ፡ ጠላቴን ፡ መተሃል (፪x)
ድል ፡ አድራጊው ፡ ኢየሱስ ፡ ክብር ፡ ይገባሃል (፪x)

የእኔ ፡ ጌታ ፡ ተባረክልኝ (፫x)
ሌላማ ፡ ምን ፡ እልሃለሁ ፡ ተባረክልኝ (፪x)

ታማኝነትህን ፡ ሁሌ ፡ አወራለሁ
ቸርነትህ ፡ ዘለዓለም ፡ ዘምራለሁ (፪x)

ሌላማ ፡ ምን ፡ እልሃለሁ ፡ ጌታዬ
ሳከብርህ ፡ ያኔ ፡ ረካለሁ ፡ አምላኬ (፪x)

ታማኝነትህን ፡ ሁሌ ፡ አወራለሁ
ቸርነትህ ፡ ዘለዓለም ፡ ዘምራለሁ (፪x)

ሌላማ ፡ ምን ፡ እልሃለሁ ፡ ጌታዬ
ሳከብርህ ፡ ያኔ ፡ ረካለሁ ፡ አምላኬ (፪x)