From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ:- መኖሪያዬ ፡ ነህ ፡ ጌታዬ
መኖሪያዬ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ (፪x)
አሳርፈኸኛል ፡ እፎይ
እፎይ ፡ ብያለሁ ፡ አንተን ፡ አግኝቻለሁ (፪x)
ወዳጅ ፡ እንደሌላቸው ፡ አልተዋችሁም ፡ አልረሳችሁም
ብለህ ፡ ተናግረሃል ፡ ያልከውን ፡ ልትፈጽም ፡ አንተ ፡ ሄደሃል
አንተ ፡ ባለህበት ፡ እኛን ፡ ልታኖረን ፡ ልታሳርፈን
በቅርብ ፡ ትመጣለህ ፡ አሜን ፡ ጌታችን ፡ ቶሎ ፡ ናልን
አዝ:- መኖሪያዬ ፡ ነህ ፡ ጌታዬ
መኖሪያዬ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ (፪x)
አሳርፈኸኛል ፡ እፎይ
እፎይ ፡ ብያለሁ ፡ አንተን ፡ አግኝቻለሁ (፪x)
በአባቴ ፡ ቤት ፡ ብዙ ፡ መኖሪያ ፡ አለ ፡ ማረፊያ ፡ አለ
ተመለሱ ፡ ይብቃ ፡ ኑ ፡ ወደ ፡ እረፍቱ ፡ ግቡ ፡ ትላለህ
ሰምቶ ፡ ላመነበት ፡ መኖሪያ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ማረፊያ ፡ አንተ ፡ ነህ
ነፍስን ፡ ከሚያጐድል ፡ ትጠብቃለህ ፡ ትጋርዳለህ
አዝ:- መኖሪያዬ ፡ ነህ ፡ ጌታዬ
መኖሪያዬ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ (፪x)
አሳርፈኸኛል ፡ እፎይ
እፎይ ፡ ብያለሁ ፡ አንተን ፡ አግኝቻለሁ (፪x)
ወዳጅ ፡ እንደሌላቸው ፡ አልተዋችሁም ፡ አልረሳችሁም
ብለህ ፡ ተናግረሃል ፡ ያልከውን ፡ ልትፈጽም ፡ አንተ ፡ ሄደሃል
አንተ ፡ ባለህበት ፡ እኛን ፡ ልታኖረን ፡ ልታሳርፈን
በቅርብ ፡ ትመጣለህ ፡ አሜን ፡ ጌታችን ፡ ቶሎ ፡ ናልን
አዝ:- መኖሪያዬ ፡ ነህ ፡ ጌታዬ
መኖሪያዬ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ (፪x)
አሳርፈኸኛል ፡ እፎይ
እፎይ ፡ ብያለሁ ፡ አንተን ፡ አግኝቻለሁ (፪x)
|