From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
በቀራንዮ ፡ መስቀል ፡ ላይ
ስራዬን ፡ አንተ ፡ ሰርተሃል
ቀንበሬን ፡ አንተ ፡ ሰበርከው
እዳዬን ፡ ከኔ ፡ አስወገድከው
ቸር ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ቸር ፡ ነህ (፪x)
ቸር ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ቸር ፡ ነህ
ቸር ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ቸር ፡ ነህ
ለኔ ፡ እንዳንተ ፡ ማን ፡ አለኝ
የውስጤ ፡ ልቤን ፡ የሚረዳልኝ
ስለኔ ፡ ሁሌ ፡ ታስባለህ
በአብ ፡ ዘንድ ፡ ለኔ ፡ ትማልዳለህ
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ቸርነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ በጐነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ምህረትህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ይቅርታህ ፡ ብዙ ፡ ነው
በደሙ ፡ አጥቦ ፡ አንጽቶ ፡ ሕይወቴንም ፡ ለውጦ
ሰው ፡ አደረገኝ ፡ ረድኤቴ ፡ እኔም ፡ ላክብረው ፡ ከልቤ (፪x)
ቸር ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ቸር ፡ ነህ
ቸር ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ቸር ፡ ነህ
ቸር ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ቸር ፡ ነህ
ቸር ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ቸር ፡ ነህ
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ቸርነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ በጐነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ምህረትህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ይቅርታህም ፡ ብዙ ፡ ነው (፪x)
|