From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ:- ባለውለታዬ ፡ ጌታዬ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ ኢየሱስ ፡ መድህኔ
ቅዱስ ፡ ስምህን ፡ እባርካለሁ
ውለታህን ፡ አስታውሰዋለሁ (፪x)
ለኔ ፡ ነው ፡ መንከራተትህ
መስቀል ፡ ተሸክመህ ፡ መውረድህ
ለኔ ፡ የደም ፡ ላብ ፡ ያላበህ
ፍቅር ፡ ነው ፡ እንዲህ ፡ ያስጨነቀህ
ውለታህን ፡ አስታውሳለሁ ፣ ፈቅጄም ፡ አመልክሃለሁ
ውለታህን ፡ አስታውሳለሁ ፣ ወድጄም ፡ አመልክሃለሁ
አዝ:- ባለውለታዬ ፡ ጌታዬ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ ኢየሱስ ፡ መድህኔ
ቅዱስ ፡ ስምህን ፡ እባርካለሁ
ውለታህን ፡ አስታውሰዋለሁ
ከአብ ፡ ዘንድ ፡ ለኔ ፡ የተሰጠ
ትልቁ ፡ ስጦታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ
ይህ ፡ ሚስጥር ፡ ለኔ ፡ ተገልጾ
መዳን ፡ ከአንተ ፡ ዘንድ ፡ ሆኖልኛል
ውለታህን ፡ አስታውሳለሁ ፣ ፈቅጄም ፡ አመልክሃለሁ
ውለታህን ፡ አስታውሳለሁ ፣ ወድጄም ፡ አመልክሃለሁ
አዝ:- ባለውለታዬ ፡ ጌታዬ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ ኢየሱስ ፡ መድህኔ
ቅዱስ ፡ ስምህን ፡ እባርካለሁ
ውለታህን ፡ አስታውሰዋለሁ (፪x)
ልከፍለው ፡ አልችልም ፡ ውለታህን
ያኔ ፡ ያረከውን ፡ በጐልጐታ
ምስጋናን ፡ ሙገሳን ፡ ይዤ
ላክብርህ ፡ ኢየሱስ ፡ ወዳጄ
ውለታህን ፡ አስታውሳለሁ ፣ ፈቅጄም ፡ አመልክሃለሁ
ውለታህን ፡ አስታውሳለሁ ፣ ወድጄም ፡ አመልክሃለሁ
አዝ:- ባለውለታዬ ፡ ጌታዬ
የእግዚአብ ሔር ፡ ልጅ ፡ ኢየሱስ ፡ መድህኔ
ቅዱስ ፡ ስምህን ፡ እባርካለሁ
ውለታህን ፡ አስታውሰዋለሁ (፪x)
|