ጸሎቴን ፡ ይሰማል (Tselotien Yesemal) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

Contact (at) Wikimezmur

አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Azeb Hailu 3.jpg


(3)

ይችላል
(Yechelal)

ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 5:46
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

የሰማያት ፡ ዳርቻ ፡ ሰሪ
የምድርም ፡ ሁሉ ፡ ፈጣሪ
አንተ ፡ አይደለህም ፡ ወይ
እግዚአብሔር ፡ ኤልሻዳይ
ኧረ ፡ አንተ ፡ አይደለህም ፡ ወይ
እግዚአብሔር ፡ ሁሉን ፡ ቻይ

አላቋርጥ ፡ ማንኳኳቴን ፡ እስኪከፈትልኝ ፡ ደጁ
ፀሎቴንም ፡ እስኪሰማ ፡ እስኪዘረጋላኝ ፡ እጁ
ዘንበል ፡ እስኪል ፡ ከዙፋኑ ፡ እስኪበዛልኝ ፡ ምሕረቱ
ዝም ፡ አልልም ፡ አላቆምም ፡ መፈለጌን ፡ ማየት ፡ ፊቱን

እግዚአብሔር ፡ በዙፋኑ ፡ ያለው
ፀሎቴን ፡ ይሰማል ፡ አውቃልሁ
አምላኬ ፡ በማደሪያው ፡ ያለው
ይራራል ፡ ይምራል ፡ አምናለሁ (፪x)

እስኪለወጥ ፡ በምስጋና ፡ የለቅሶ ፡ የእንባ ፡ ጩኸቴ
ሙሉ ፡ ሆኖ ፡ እንኪመጣ ፡ እስኪለቀቅ ፡ በረከቴ
ከአንደበቱ ፡ እስኪወጣ ፡ የበረከት ፡ ንግግር
አልነሳም ፡ ዞር ፡ አልልም ፡ ከዙፋኑ ፡ ከእግሩ ፡ ስር

እግዚአብሔር ፡ በዙፋኑ ፡ ያለው
ፀሎቴን ፡ ይሰማል ፡ አውቃልሁ
አምላኬ ፡ በማደሪያው ፡ ያለው
ይራራል ፡ ይምራል ፡ አምናለሁ (፪x)

የተስፋውን ፡ ቃል ፡ አስቦ ፡ ሊፈጽመው ፡ እስኪነሣ
የምድሬኔም ፡ ኃጢአት ፡ በደል ፡ ይቅር ፡ ብሎ ፡ እስኪረሳ
ክብሩን ፡ ዳግም ፡ እስኪመልስ ፡ በቅዱሱ ፡ ማደሪያው
አላቆምም ፡ ክርክሬን ፡ እስኪነሣ ፡ ከስፍራው

የሚሰማ ፡ የሚመልስ ፡ የሚምር ፡ ነው ፡ የሚራራ (፪x)
በጎነቱ ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ በሞገሱ ፡ የተፈራ (፪x)
ቸር ፡ እንደእርሱ ፡ ስለሌለ ፡ በምድር ፡ ቢሆን ፡ በሰማይ (፪x)
አንዲቷም ቀን አታልፍብኝ ፡ ያምላኬን ፡ ፊቱን፡ ሳላይ (፬x)