From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ሕያው አምላክ ነህ (x3)
ዛሬም ደምቅህ ያለህ
ቅዱስ አምላክ ነህ (x3)
ዛሬም ከብረህ ያለህ
ሕያው...
ቅዱስ...
አትወርድም ከከፍታህ
አትሻር ከስልጣንህ
አምላኬ ሕያው ነህ
አትደክምም ክጉልበትህ
አትዝልም ከብርታትህ
ጌታዬ ሕያው ነህ
አትወርድም...
አትደክምም...
ሕያው...
ቅዱስ...
አንተን ሰማይንና ምድሩን
የሰራኸውን አምላክ አመልካለሁ
እኔ አመልካለሁ
አንተን ባህሩን እና የብሱን
የሰራኸውን አምላክ አመልካለሁ
እኔ አመልካለሁ
እኔ አንተን ትልቁን እና ትንሹን
የሰራኸውን አምላክ አመልካለሁ
እኔ አመልካለሁ
ኧረ አንተን የቅርቡን እና የሩቁን
የሰራኸውን አምላክ አመልካለሁ
እኔ አመልካለሁ
የተፈራ የተፈራ የተፈራ ነው
የከበረ የከበረ የከበረ ነው (x2)
ትናንትናም ዛሬም ነገም ለዘላለም
እንደ ጌታ እንደ ኢየሱስ ያለ የለም (x2)
መገረሚያዬ
መደነቂያዬ
መሽቶ ሲነጋ
ዜማ እልልታዬ
ኢየሱስ ጌታዬ
|