በዙፋኑ ፡ ላይ (Bezufanu Lay) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Lyrics.jpg


(5)

በመጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር
(Bemejemeria Egziabhier)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፱ (2017)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 5:04
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

በዙፋኑ ፡ ላይ ፡ በማደሪያው ፡ ላይ
በክብርና ፡ በግርማው
ሳይለዋወጥ ፡ ሳይነዋወጥ
እንዲሁ ፡ እንደጵና ፡ ያለው
ከነችሎቱ ፡ ከነብርታቱ ፡ የሚኖረው
ኧረ ፡ ይሄ ፡ ማነው
የአማልክት ፡ አምላክ ፡ የጌቶች ፡ ጌታ ፡
እግዚአብሔር ፡ እርሱ ፡ የእኔ ፡ አምላክ ፡ ነው

እግሮቹ ፡ በደመናት ፡ ላይ ፡ ይራመዳሉ
ዓይኖቹ ፡ በምድር ፡ ዙሪያ ፡ ሁሉ ፡ ያያሉ
አይገለጥም ፡ በቋንቋ ፡ ታላቅነቱ
እኔ ፡ ክብር ፡ እሰጣለው ፡ ለጌትነቱ
አይገለጥም ፡ በቋንቋ ፡ ታላቅነቱ
እኔ ፡ ስግደት ፡ አበዛለው ፡ ለጌትነቱ

ፍጥረት ፡ የሚሰማው ፡ የሚወደው
ገና ፡ ሳይነጋ ፡ በማለዳው
እግዚአብዜር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ
የሚለውን ፡ ቃል ፡ በመሆኑ
እኔም ፡ ልዘምር ፡ ይህንኑ
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ
እኔም ፡ ልዘምር ፡ ይህንኑ
አምላኬ ፡ አለ ፡ በዙፋኑ ፪

በክብር ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ከብሯል
በኃይል ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ኃይሏል ፡
በሥልጣን ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ተሹሟል
በሞገስ ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ደምቋል ፡
በዝና ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ታውቋል ፡
ኢየሱስ ፡ ከሁሉም ፡ ይልቃል ፭

ማደሪያው ፡ የተለየ ፡ ነው ፡ ከአማልክት ፡ ሁሉ
ለዘለዓለም ፡ የሚኖር ፡ በሙሉ ፡ ኃይሉ
ባለግርማና ፡ ሞገስ ፡ የክብር ፡ ጌታ
ምሥጋና ፡ ክብር ፡ አምልኮ ፡ ይብዛለት ፡ ዕልልታ
ባለግርማና ፡ ሞገስ ፡ የክብር ፡ ጌታ
ምሥጋና ፡ ክብር ፡ አምልኮ ፡ ይብዛለት ፡ ዕልልታ

በዙፋኑ ፡ ላይ ፡ በማደሪያው ፡ ላይ
በክብርና ፡ በግርማው
ሳይለዋወጥ ፡ ሳይነዋወጥ
እንዲሁ ፡ እንደጵና ፡ ያለው
ከነችሎቱ ፡ ከነብርታቱ ፡ የሚኖረው
ኧረ ፡ ይሄ ፡ ማነው
የአማልክት ፡ አምላክ ፡ የጌቶች ፡ ጌታ ፡
እግዚአብሔር ፡ እርሱ ፡ የእኔ ፡ አምላክ ፡ ነው

በክብር ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ከብሯል
በኃይል ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ኃይሏል ፡
በሥልጣን ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ተሹሟል
በሞገስ ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ደምቋል ፡
በዝና ፡ ማን ፡ እንደርሱ ፡ ታውቋል ፡
ኢየሱስ ፡ ከሁሉም ፡ ይልቃል ፭

በዙፋኑ ፡ ላይ ፡ በማደሪያው ፡ ላይ
በክብርና ፡ በግርማው
ሳይለዋወጥ ፡ ሳይነዋወጥ
እንዲሁ ፡ እንደጵና ፡ ያለው
ከነችሎቱ ፡ ከነብርታቱ ፡ የሚኖረው
ኧረ ፡ ይሄ ፡ ማነው
የአማልክት ፡ አምላክ ፡ የጌቶች ፡ ጌታ ፡
እግዚአብሔር ፡ እርሱ ፡ የእኔ ፡ አምላክ ፡ ነው