በርታ (Berta) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Lyrics.jpg


(5)

በመጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር
(Bemejemeria Egziabhier)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፱ (2017)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 5:32
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

በሕይወት ፡ ጉዞ ፡ ላይ ፡
ቢያደከም ፡ መንገዱ ፡
የፈተናው ፡ ብዛት ፡ ዉጣ ፡ ውረዱ
ግን ፡ የያዝከው ፡ ተስፋ ፡
ከአምላህ ፡ ከጌታ
የጰና ፡ ነውና ፡ ወገኔ ፡ በርታ (2x)

ምናልባትም ፡ በጊዜያዊ ፡ ፈተና ፡ ተጨቀሃል
በብዙማ ፡ በብዙ ፡ ሃዘን ፡ በቅሶ ፡ ውስጥ ፡ አልፈሃል
ግን ፡ ያሁኑ ፡ የሚያበቃ ፡ የሚያከትም ፡ የሚያልፍ ፡ ነውና
ለዘላለም ፡ የፅና ፡ የሕይወት ፡ ቃል ፡ አለህና

አይዞህ ፡ በርታ ፡ ጭክን ፡ በል ፡ በእምነት ፡ ፅና
እመጣለሁ ፡ ያለህ ፡ ጌታ ፡ ይመጣልና(2x)

በምድር ፡ ላይ ፡ የሰው ፡ ሕይወት ፡ ሰልፍ ፡ ነው ፡ የጦር ፡ ሜዳ
ሕይወት ፡ ሩጫ ፡ ለማዘግየት ፡ የሚጥር ፡ የሚጐዳ
ጦርነቱን ፡ ለማሸነፍ ፡ ብትፈልግ ፡ ልትረታ
አስተውለው ፡ የሰጠህን ፡ ክቡር ፡ ቃል ፡ የአንተ ፡ ጌታ

አይዞህ ፡ በርታ ፡ ጭክን ፡ በል ፡ በእምነት ፡ ፅና
እመጣለሁ ፡ ያለህ ፡ ጌታ ፡ ይመጣልና(2x)

አለኝ ፡ ያልከው ፡ በጅህ ፡ ያለው ፡ ተበትኖ ፡ ቢጠፋ
ግራ ፡ ቀኙ ፡ ቢዘጋብህ ፡ ብታጣ ፡ የሚሆን ፡ ተስፋ
ሰማያትን ፡ ምድርን ፡ የሰራው ፡ ጌታ ፡ ረዳትህ
ብሰማው ፡ ብትፈቅድ ፡ ለአፍታ ፡ ጊዜ ፡ ሰተህ

አይዞህ ፡ በርታ ፡ ጭክን ፡ በል ፡ በእምነት ፡ ፅና
እመጣለሁ ፡ ያለህ ፡ ጌታ ፡ ይመጣልና(2x)

በሕይወት ፡ ጉዞ ፡ ላይ ፡
ቢያደከም ፡ መንገዱ ፡
የፈተናው ፡ ብዛት ፡ ዉጣ ፡ ውረዱ
ግን ፡ የያዝከው ፡ ተስፋ ፡
ከአምላህ ፡ ከጌታ
የፀና ፡ ነውና ፡ ወገኔ ፡ በርታ