በመጀመሪያ (Bemejemeria) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Lyrics.jpg


(5)

በመጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር
(Bemejemeria Egziabhier)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፱ (2017)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 6:28
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

የእግዚያብሔር ፡ ግርማ ፡ ክብርና ፡ ሞገሱ
በፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ ላይ ፡ ታይቶ ፡ ያወራል ፡ ስለእርሱ
ፍቅሩ ፡ ርህራሄው ፡ ቸርነት ፡ ምሕረቱ
ሁሉም ፡ ይዘምራል ፡ በዜማ ፡ አንደበቱ
ሁሉን ፡ ቻይነቱ

ሳይሆን ፡ ገና ፡ ሰማይ ፡ ሳይሆን ፡ ገና ፡ ምድር
መጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነበር
በላይ ፡ እና ፡ በታች ፡ የሚባል ፡ ሳይኖር
አስቀድሞ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነበር
ሳትታይ ፡ ጨረቃ ፡ ሳትበራ ፡ ፀሐይ
እግዚአብሔር ፡ አምላክ ፡ ቀድሞ ፡ አልነበረ ፡ ወይ
ጥዋት ፡ እና ፡ ማታ ፡ ተብሎም ፡ ሳይለይ
በሥልጣን ፡ በክብር ፡ እርሱ ፡ አልነበር ፡ ወይ

አዝ፦ በመጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር ፡ በመጀመሪያ
በመጀመሪያ ፡ የእኔ ፡ አምላክ ፡ በመጀመሪያ
ከሁሉ ፡ በፊት ፡ እግዚአብሔር ፡ ከሁሉ ፡ በላይ
ነበር ፡ እርሱ ፡ መጀመሪያ ፡ ሃሌሉያ (፪x)

ለነበረው ፡ ላለው ፡ ለሚኖረው
ሕያው ፡ አምላክ ፡ ልዑል ፡ እግዚአብሔር
የሰራችሁ ፡ ፍጥረታት ፡ በሙሉ
በመገዛት ፡ አሜን ፡ ክበር ፡ በሉ (፪x)

የውሃው ፡ ክምችት ፡ ሳይባል ፡ ባሕር
መጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነበር
ምድርም ፡ ሳታበቅ ፡ ቡቃያና ፡ ሳር
አስቀድሞ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነበር
ሳይለዩ ፡ ገና ፡ ውሃና ፡ መሬቱ
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በኃይል ፡ በችሎቱ
እለታት ፡ ዓመታት ፡ ዘመናት ፡ ሳይሆኑ
እርሱ ፡ እንዳለ ፡ አለ ፡ በክብር ፡ ዙፋኑ

አዝ፦ በመጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር ፡ በመጀመሪያ
በመጀመሪያ ፡ የእኔ ፡ አምላክ ፡ በመጀመሪያ
ከሁሉ ፡ በፊት ፡ እግዚአብሔር ፡ ከሁሉ ፡ በላይ
ነበር ፡ እርሱ ፡ መጀመሪያ ፡ ሃሌሉያ (፪x)

ሳይሰራ ፡ አዳም ፡ ሳትመጣ ፡ ሄዋን
መጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነበር
እፍ ፡ ሳይልበት ፡ ገና ፡ እስትንፋሱን
አስቀድሞ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነበር
ሳይባሉ ፡ ገና ፡ ብዙ ፡ እና ፡ ተባዙ
ምድርን ፡ አስተዳድሩ ፡ ፍጥረታትን ፡ ግዙ
አዳም ፡ ሕያው ፡ ሆኖ ፡ ሳይመላለስ
በማደሪያው ፡ አለ ፡ የክብር ፡ ንጉሥ
ስሙም ፡ ቅዱስ

አዝ፦ በመጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር ፡ በመጀመሪያ
በመጀመሪያ ፡ የእኔ ፡ አምላክ ፡ በመጀመሪያ
ከሁሉ ፡ በፊት ፡ እግዚአብሔር ፡ ከሁሉ ፡ በላይ
ነበር ፡ እርሱ ፡ መጀመሪያ ፡ ሃሌሉያ (፪x)

ለነበረው ፡ ላለው ፡ ለሚኖረው
ሕያው ፡ አምላክ ፡ ልዑል ፡ እግዚአብሔር
የሰራችሁ ፡ ፍጥረታት ፡ በሙሉ
 በመገዛት ፡ አሜን ፡ ክበር ፡ በሉ (፪x)