ሰው ፡ ነኝና (Sew Negnena) - አውታሩ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አውታሩ ፡ ከበደ
(Awtaru Kebede)

Awtaru Kebede 5.jpeg


(5)

ይቅርታ
(Yeqerta)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 4:32
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአውታሩ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Awtaru Kebede)

አንዳንዴማ
ሆዴን ፡ ባር ፡ ባር ፡ ሲለው ፡ ብቸኝነት ፡ ይዞኝ
አንዳንዴማ
የልብ ፡ ወዳጅ ፡ ያልኩት ፡ ከጐኔ ፡ ሲርቀኝ (፪x)

አዝናለሁ ፡ ሰው ፡ ነኝና (፪x)
የቀረው ፡ ግን ፡ ይቅርብኝ
አስቤ ፡ ልበል ፡ ቀና (፪x)

በዚህ ፡ ዓለም ፡ ስኖር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
አንዴ ፡ ይሞላል ፡ ይጐላል
አንተ ፡ ከጐኔ ፡ ስላለህ ፡ ምን ፡ ያሰጋኛል (፪x)

አሃ ፡ አንዴ ፡ ይሞላል ፡ አንዴ ፡ ይጐላል ፡ አሃሃ
አንተ ፡ ስላለህ ፡ ምን ፡ ያሰጋኛል
አሃ ፡ ቀኑ ፡ ይመሻል ፡ ቀኑ ፡ ይነጋል ፡ አሃሃ
አንተ ፡ ስላለህ ፡ ምን ፡ ያሰጋኛል

ጐዳናው ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ በሰው
በሰው ፡ ልብ ፡ ውስጥ ፡ ያለው
ትላንትናን ፡ ኖሮ ፡ ዛሬ ፡ ምኞት ፡ አለው (፪x)

ደግሞ ፡ ይናፍቀኛል ፡ ፊትህ ፡ ይናፍቀኛል (፬x)

አንዳንዴማ
ሆዴን ፡ ባር ፡ ባር ፡ ሲለው ፡ ብቸኝነት ፡ ይዞኝ
አንዳንዴማ
የልብ ፡ ወዳጅ ፡ ያልኩት ፡ ከጐኔ ፡ ሲርቀኝ (፪x)

አዝናለሁ ፡ ሰው ፡ ነኝና (፪x)
የቀረው ፡ ግን ፡ ይቅርብኝ
አስቤ ፡ ልበል ፡ ቀና (፪x)