የምስራች (Yemeserach) - አዲስ ፡ አበባ ፡ አማኑኤል ፡ ህብረት

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲስ ፡ አበባ ፡ አማኑኤል ፡ ህብረት
(Addis Ababa Amanuel Hebret)

Lyrics.jpg


(1)

ታማኝ ፡ ነው ፡ እግዚአብሔር
(Tamagn New Egziabhier)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፮ (2004)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲስ ፡ አበባ ፡ አማኑኤል ፡ ህብረት ፡ አልበሞች
(Albums by Addis Ababa Amanuel Hebret)

የምስራች ፡ የምትነግሪ ፡ ፅዮን ፡ ሆይ
ከፍ ፡ ወዳለው ፡ ተራራ ፡ ውጪ
አትቆጥቢ ፡ ድምጽሽንም ፡ አሰሚ (፪x)

እነሆ ፡ አምላክሽ ፡ ሊያከብርስ ፡ ወዷል
የክብርን ፡ ካባ ፡ ባንቺ ፡ ላይ ፡ ጥሏል
ነገሥታት ፡ ሁሉ ፡ ላንቺ ፡ ይሰግዳሉ
አሕዛብ ፡ ፊትሽ ፡ ይዋረዳሉ

ሙላት ፡ አድርጐ ፡ ልጁን ፡ ሰጥቶሻል
ስለዚህ ፡ ፅዮን ፡ ምን ፡ ያሰጋሻል
በተራሮች ፡ ላይ ፡ በድል ፡ ቁሚና
ምድሪቱን ፡ ሙይ ፡ ገዢ ፡ ሁኝና

መቅረዞችሽም ፡ ዘይትን ፡ ይሙሉ
በክብርም ፡ ላይ ፡ ክብር ፡ ይጨምሩ
ለሰጠሽ ፡ ተስፋ ፡ ፍፃሜ ፡ አለና
ተነሺ ፡ ፅዮን ፡ አብሪ ፡ እንደገና

ፍጥረት ፡ ተጨንቆ ፡ በብዙ ፡ ውጥረት
ይጠባበቃል ፡ የአንቺን ፡ መገለጥ
ገዢ ፡ ሁኚና ፡ ከሁሉ ፡ የበላይ
ፅዮን ፡ ተነሺ ፡ በምድሪቱ ፡ ላይ (፪x)