አባል:Tarekegn Hadaro
የገነባውን ፡ አፈራረሰ
የጠለለውን ፡ አደፈረሰ የተከለውን ፡ ነቅሎ ፡ ጣለና የእግዚአብሔርን ፡ ቤት ፡ አስቀረው ፡ ኦና::
ያንን ፡ ሰው ፡ 4 ጌታ ፡ መልሰው
ድንግሉን ፡ መሬት ፡ አርሶ ፡ ጎልጉሎ በብዙ ፡ ድካም ፡ ዘሩን ፡ በትኖ ግን ፡ አልታገሰም ፡ ሮጦ ፡ ፈርጥጡዋል የተዘራው ፡ ዘር ፡ በአረም ፡ ተውጥዋል::
ያንን ፡ ሰው ፡ 4 ጌታ ፡ መልሰው::
በዓለም ፡ ተንቆ ፡ ሞኝ ፡ ተብሎ ፡ ስድብ ፡ ግልምጫውን ፡ ነቀፋ ፡ ችሎ ፡ አክሊል ፡ ሊሰጠው ፡ ጌታ ፡ ሲመጣ ፡ ኮብልሎ ፡ ኖሮ ፡ ከቦታው ፡ ታጣ ::
ያንን ፡ ሰው ፡ 4 ጌታ ፡ መልሰው
ህዝብን ፡ ሊጠብቅ ፡ መንጋን ፡ ሊመራ ፡ በመከር ፡ ጊዜ ፡ ዘር ፡ እንድዘራ ፡ መክሊት ፡ ሰጥተሄው ፡ አልነበረም ፡ ወይ ታዲያ ፡ ያንን ፡ ሰው ፡ አትመልሥም ፡ ወይ::