አልተወውም (Altewewm) - ዜማ ፡ ለክርስቶስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዜማ ፡ ለክርስቶስ
(Zema 4 Christ)

Zema 4 Christ 2.jpg


(2)

ክቡር ፡ ቀን
(Kebur Qen)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2013)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 5:37
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዜማ ፡ ለክርስቶስ ፡ አልበሞች
(Albums by Zema 4 Christ)

"አልተወውም ፡ አለቀውም ፡ መድሃኒቴን
የሰላሜን ፡ ጌታ ፡ እረፍት ፡ የሰጠኝን
ጌታ ፡ ኢየሱስን ፡ ኦሆሆ"

አዝ፦ አልተወውም ፡ አለቀውም ፡ መድሃኒቴን
የሰላሜን ፡ ጌታ ፡ እረፍት ፡ የሰጠኝን
ጌታ ፡ ኢየሱስን (፪x)

መግቢያ ፡ መውጫ ፡ አጥቼ ፡ ስንከራተት ፡ በዓለም
አጽናናኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ነይ ፡ የእኔ ፡ ነሽ ፡ አለኝ
ጥሪውንም ፡ ሰማሁ ፡ ሕይወቴም ፡ ረካሁ
መቅበዝበዜም ፡ ቀረ ፡ ነፍሴም ፡ ተደሰተች

አዝ፦ አልተወውም ፡ አለቀውም ፡ መድሃኒቴን
የሰላሜን ፡ ጌታ ፡ እረፍት ፡ የሰጠኝን
ጌታ ፡ ኢየሱስን

ኃያሉ ፡ አምላክ ፡ ነው ፡ ለእኔ ፡ የደረሰው
ማቄን ፡ የቀደደ ፡ እንባዬን ፡ ያበሰው
ሰላም ፡ ኧረፍት ፡ ሰጥቶኝ ፡ መድሃኒት ፡ የሆነኝ
ተስፋዬን ፡ አድሶ ፡ በቃሉ ፡ ያጸናኝ

አዝ፦ አልተወውም ፡ አለቀውም ፡ መድሃኒቴን
የሰላሜን ፡ ጌታ ፡ እረፍት ፡ የሰጠኝን
ጌታ ፡ ኢየሱስን ፡ ኦሆሆ

ለነፍሴ ፡ እረፍት ፡ ሆነ ፡ ቀለለ ፡ ሸክሜ
መጨነቄ ፡ ቀረ ፡ ፈሰሰ ፡ ሰላሜ
ፀጋን ፡ አለበሰኝ ፡ ነውሬንም ፡ ሸፈነ
ልገዛለት ፡ እንጂ ፡ እርሱን ፡ እንዴት ፡ ልተው (፪x)

አዝ፦ አልተወውም ፡ አለቀውም ፡ መድሃኒቴን
የሰላሜን ፡ ጌታ ፡ እረፍት ፡ የሰጠኝን
ጌታ ፡ ኢየሱስን