አመልካለሁ (Amelkalehu) - ዜማ ፡ ለክርስቶስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዜማ ፡ ለክርስቶስ
(Zema 4 Christ)

Zema 4 Christ 1.jpg


(1)

በማመኔ ፡ ብቻ
(Bemamenie Bicha)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ (2007)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 6:22
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዜማ ፡ ለክርስቶስ ፡ አልበሞች
(Albums by Zema 4 Christ)

 
ነፍሴን ፡ ማርከህ ፡ ገዝተኀኛል ፡ በፍቅርህ
ስለእኔ ፡ በደል ፡ ዋጋ ፡ ከፍለሃል
ዛሬ ፡ እኔ ፡ ለአንተ ፡ ብዘምር ፡ ያንስሃል
ፍቅርህን ፡ ለመግለጽ ፡ ለእኔ ፡ ሞተሃል

አዝ:- አመልካለሁ ፡ እስከ ፡ ሕይወቴ ፡ ፍጻሜ
ቤትህ ፡ ይሁን ፡ የመጨረሻዬ
አንተን ፡ ትቼ ፡ አማራጭ ፡ አላይም ፡ አላገኝም
ዘለዓለም

ምንም ፡ የለም ፡ ለአንተ ፡ ያደረኩት ፡ ዉለታ
ምላሽ ፡ የሚሆን ፡ ፍቅርህን ፡ የሚተካ
በፊትህ ፡ መቆም ፡ ማይገባኝ ፡ ነበርኩኝ
ግን ፡ በደም ፡ ገዝተህ ፡ ልጅህ ፡ አደረከኝ

አዝ:- አመልካለሁ ፡ እስከ ፡ ሕይወቴ ፡ ፍጻሜ
ቤትህ ፡ ይሁን ፡ የመጨረሻዬ
አንተን ፡ ትቼ ፡ አማራጭ ፡ አላይም ፡ አላገኝም
ዘለዓለም

የፍቅር ፡ አምላክ ፡ ነህ
(ነፍስህን ፡ የሰጠህ) ነፍስህን ፡ የሰጠህ ፡ ስለእኔ
(ራስህን ፡ አዋርደህ) ራስህን ፡ አዋርደህ
አጸዳህ ፡ በደሌን
ስለዚህ ፡ በሕይወት ፡ በኑሮዬ
አንተን ፡ አከብራለሁ
ለዘለዓለም ፡ አሜን

አዝአመልካለሁ (፱x) (አማራጭ ፡ አላይም ፡ አላገኝም)
ዘለዓለም

አመልካለሁ (፪x) ጌታ
ከአንተ ፡ ወዴት ፡ እሄዳለሁ
አመልክሃለሁ (፪x)