Yoseph Ayalew/Serayien Yeserahelegn/Temechegn Bieteh

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ዘማሪ ዮሴፍ አያሌው

አልበም ሥራዬን የሠራህልኝ


ሥምህ ጋሻዬና ከለላዬ።

ሆኖልኛል ጌታ በዘመኔ።

ሳልሰጋ እኖራለው ልቤ እርፎ።

በኃያሉ ክንድህ ተደግፎ (፪x)።


ክበር አንተ ብቻ (፪x) የለህ አቻ።

ንገሥ አንተ ብቻ (፪x) የለህ አቻ።

ግዛኝ አንተ ብቻ (፪x) የለህ አቻ።


አዝ

ተመቸኝ ቤትህ ተመቸኝ።

ተመችኝ ጉያህ ተመቸኝ።


አልመለስም ወደ ኋላ።

የግብጽን ሽንኩርት ላልበላ።

ቃልኪዳን ገባሁ ለእራሴ።

አመልክሃለሁ ኢየሱሴ (፪x)።


እንደሚፈስ ዘይት ነው ሥምህ።

ስለዚህ ደናግል ወደዱህ።

እኔም አንተን አንተኑ ብያለሁ።

ስምህን ላከብር ይሄው ቆሜያለሁ (፪x)።


ክበር አንተ ብቻ (፪x) የለህ አቻ።

ንገሥ አንተ ብቻ (፪x) የለህ አቻ።

ግዛኝ አንተ ብቻ (፪x) የለህ አቻ።


አልመኝ ከአንተ በስተቀር።

አያምረኝም ያለው በምድር።


ቀምሼ አውቄሃለሁ።

ምርጫዬ አድርጌሃለሁ።

የሕይወቴ መደምደሚያ ነህ።

ዘለዓለም ጌታዬ ትበቃኛለህ (፪x)።


ክበር አንተ ብቻ (፪x) የለህ አቻ።

ንገሥ አንተ ብቻ (፪x) የለህ አቻ።

ግዛኝ አንተ ብቻ (፪x) የለህ አቻ።


አዝ

ተመቸኝ ቤትህ ተመቸኝ።

ተመችኝ ጉያህ ተመቸኝ።


አልመለስም ወደ ኋላ።

የግብጽን ሽንኩርት ላልበላ።

ቃልኪዳን ገባሁ ለእራሴ።

አመልክሃለሁ ፡ ኢየሱሴ (፪x)።