ሰው ፡ አይረሳም (Sew Ayresam) - ዮሴፍ ፡ አያሌው

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
ዮሴፍ ፡ አያሌው
(Yoseph Ayalew)

Yoseph Ayalew 2.jpeg


(2)

ሥራዬን ፡ የሠራህልኝ
(Serayien Yeserahelegn)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፭ (2002)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 7:29
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ አያሌው ፡ አልበሞች
(Albums by Yoseph Ayalew)

አዝ፦ ሰው ፡ አይረሳም ፡ ጌታ
ሰው ፡ አይረሳም ፡ ኢየሱስ (፪x)

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ጌታ
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ኢየሱስ (፪x)

ፍቅሩ ፡ አይቀዘቅዝ ፡ ወረት ፡ አያውቀው
እንደ ፡ ጌታ ፡ ያለ ፡ የትም ፡ አይገኝም
የተናገረውን ፡ ቃሉ ፡ ይፈጽማል
ተናግሮ ፡ ማድረግ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ያውቃል

አዝ፦ ሰው ፡ አይረሳም ፡ ጌታ
ሰው ፡ አይረሳም ፡ ኢየሱስ (፪x)

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ጌታ
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ኢየሱስ (፪x)

ማክበርና ፡ ማንሳት ፡ ጌታ ፡ ያውቅበታል
እርሱን ፡ የተጠጋ ፡ የቱ ፡ መሽቶበታል
እንደ ፡ ንጋት ፡ ብርሃን ፡ ክብሩ ፡ እየጨመረ
አቀማጥሎ ፡ ያኖራል ፡ እንዲህ ፡ እያከበረ

አዝ፦ ሰው ፡ አይረሳም ፡ ጌታ
ሰው ፡ አይረሳም ፡ ኢየሱስ (፪x)

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ጌታ
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ኢየሱስ (፪x)

የቱነው ፡ የተረሳ ፡ ማነው ፡ የሚጸጸት
ሳይታሰብ ፡ ኖሮ ፡ ጊዜው ፡ ያለፈበት
የተጣለው ፡ ይልቅ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ አድርጐ
ደስታ ፡ ይሰጠዋል ፡ እንባን ፡ ከዓይኑ ፡ ጠርጐ

አዝ፦ ሰው ፡ አይረሳም ፡ ጌታ
ሰው ፡ አይረሳም ፡ ኢየሱስ (፪x)

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ጌታ
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ኢየሱስ (፪x)

አይጠረጠርም ፡ ይታመናል ፡ እንጂ
እንኳን ፡ ቤቱ ፡ ኖሮ ፡ አድጐ ፡ በእርሱ ፡ እጂ
ያሳልፍለታል ፡ ዘመኑን ፡ በተድላ
እርዳኝ ፡ ብሎ ፡ መጥቶ ፡ የቱ ፡ ሰው ፡ ተጐዳ

አዝ፦ ሰው ፡ አይረሳም ፡ ጌታ
ሰው ፡ አይረሳም ፡ ኢየሱስ (፪x)

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ጌታ
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ኢየሱስ (፪x)