Yoseph Ayalew/Serayien Yeserahelegn/Serayien Yeserahelegn

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ዘማሪ ዮሴፍ አያሌው ርዕስ=ሥራዬን የሠራህልኝ

አዝ ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ (፪x) አማኑኤል ከፍ ፡ በልልኝ (፫x) ኢየሱሴ ከፍ በልልኝ የእኔ ጌታ ከፍ በልልኝ

ተራራውን ንዶ ሜዳ ከአደረገው መራመድ ብቻ ነው ከእኔ ሚጠበቀው (፪x)

ጐዳናዬ ቀንቶ ተራመድ ብሎኛል ከእኔ ጋር ስላለ ማን ይቃወመኛል (፪x)

ማን ይቃወመኛል (፪x) የቱ ይይዘኛል (፪x)

አልፈራም ልቤ አይሰጋ ጌታዬ አለ ከእኔ ጋ አልፈራም ልቤ አይሰጋ የጠራኝ አለ ከእኔ ጋ አይቆምም ምንም ከፊቴ እግዚአብሔር ነው ዛሬም ጉልበቴ (፭x)

አዝ ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ (፪x) አማኑኤል ከፍ በልልኝ (፫x) ኢየሱሴ ከፍ በልልኝ የእኔ ጌታ ከፍ በልልኝ

ሰባሪው እግዚአብሔር ከፊት ወጥቷልና ሃሳቤ ተሳክቶ መንገዴም ተቃና (፪x)

የነሃሱን ደጆች በስልጣን ሰበረው እኔም ሰባብሬ ከእርሱ ጋር አልፌያለው (፪x)

ከእርሱ ጋር አልፌያለው (፬x)

አልዝልም እኔ አልደክምም ስራዬ አያሰለችም (፪x)

ቅባቱ በእኔ ስላለ ይሄዳል እየጨመረ (፭x) አዝ ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ (፪x) አማኑኤል ከፍ በልልኝ (፫x) ኢየሱሴ ከፍ በልልኝ የእኔ ጌታ ከፍ በልልኝ

ታማኝ ነው የጠራኝ ጌታ ለምንም ትጥቄ አይፈታ (፪x)

ብርቱ ነው በቃሉ የፀና ይመራኛል በድል ጐዳና (፭x) አዝ ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ (፪x) አማኑኤል ከፍ በልልኝ (፫x) ኢየሱሴ ከፍ በልልኝ የእኔ ጌታ ከፍ በልልኝ

ከፍ በል ብል ሁልጊዜ ይሄ መች ይበቃሃል (፫x) ተባረክ ብል ሁልጊዜ ይሄ መች ይበቃሃል (፫x) ተመለክ ብል ሁልጊዜ ይሄ መች ይበቃሃል (፫x)