Yoseph Ayalew/Serayien Yeserahelegn/Serayien Yeserahelegn

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ

ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ

አማኑኤል ከፍ በልልኝ

አማኑኤል ከፍ በልልኝ

ኢየሱሴ ከፍ በልልኝ

የእኔ ጌታ ከፍ በልልኝ

ተራራውን ንዶ ሜዳ ካደረገው

መራመድ ብቻ ነው ከእኔ ሚጠበቀው

ተራራውን ንዶ ሜዳ ካደረገው

መራመድ ብቻ ነው ከእኔ ሚጠበቀው


ጐዳናዬ ቀንቶ ተራመድ ብሎኛል

ከእኔ ጋር ስላለ ማን ይቃወመኛል

ጐዳናዬ ቀንቶ ተራመድ ብሎኛል

ከእኔ ጋር ስላለ ማን ይቃወመኛል

ማን ይቃወመኛል

ማን ይቃወመኛል

የቱ ይይዘኛል

የቱ ይይዘኛል


አልፈራም ልቤ አይሰጋ ጌታዬ አለ ከእኔ ጋ

አልፈራም ልቤ አይሰጋ የጠራኝ አለ ከእኔ ጋ

አይቆምም ምንም ከፊቴ እግዚአብሔር ነው ዛሬም ጉልበቴ

እግዚአብሔር ነው ዛሬም ጉልበቴ (4)

ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ (2)

አማኑኤል ከፍ በልልኝ (2)

ኢየሱሴ ከፍ በልልኝ

የእኔ ጌታ ከፍ በልልኝ


ሰባሪው እግዚአብሔር ከፊት ወጥቷልና

ሃሳቤ ተሳክቶ መንገዴም ተቃና

ሰባሪው እግዚአብሔር ከፊት ወጥቷልና

ሃሳቤ ተሳክቶ መንገዴም ተቃና

የነሃሱን ደጆች በስልጣን ሰበረው

እኔም ሰባብሬ ከእርሱ ጋር አልፌያለው

ከእርሱ ጋር አልፌያለው(4)


አልዝልም እኔ አልደክምም ስራዬ አያሰለችም

አልዝልም እኔ አልደክምም ስራዬ አያሰለችም

ቅባቱ በእኔ ስላለ ይሄዳል እየጨመረ

ይሄዳል እየጨመረ(4)


ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ....


ታማኝ ነው የጠራኝ ጌታ ለምንም ትጥቄ አይፈታ

ታማኝ ነው የጠራኝ ጌታ ለምንም ትጥቄ አይፈታ

ብርቱ ነው በቃሉ የፀና ይመራኛል በድል ጐዳና

ይመራኛል በድል ጐዳና(4)

ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ....

ከፍ በል ብል ሁልጊዜ ይሄ መች ይበቃሃል ይሄ መች ይበቃሃል ይሄ መች ይበቃሃል

ተባረክ ብል ሁልጊዜ ይሄ መች ይበቃሃል ይሄ መች ይበቃሃል ይሄ መች ይበቃሃል

ተመለክ ብል ሁልጊዜ ይሄ መች ይበቃሃል ይሄ መች ይበቃሃል ይሄ መች ይበቃሃል