Yoseph Ayalew/Serayien Yeserahelegn/Anten Keyaze Sew

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ዘማሪ ዮሴፍ አያሌው ርዕስ አንተን ከያዘ ሰው አልበም ሥራዬን የሠራህልኝ

አዝ አንተን ከአገኘ ሰው ምን ይሆናል (፫x) አንተን ከያዘ ሰው ምን ይሆናል (፫x) የልቤ ማረፊያ ነህ የማምለጫ አለቴ እኮራብሃለሁኝ ኢየሱስ መድሃኒቴ (፪x)

አባትስ ማለት እንደ አንተ ነው ወዳጅስ ማለት እንደ አንተ ነው አሳድገኽኛል ከእጅህ እየበላሁ ሰው የሆንኩት በአንተ ነው ይህንን ልቤ አልረሳው (፬x)

አዝ አንተን ከአገኘ ሰው ምን ይሆናል (፫x) አንተን ከያዘ ሰው ምን ይሆናል (፫x) የልቤ ማረፊያ ነህ የማምለጫ አለቴ እኮራብሃለሁኝ ኢየሱስ መድሃኒቴ (፪x)

ዘመን ሲከፋ ሲቀያየር አንተ ግን ያው ነህ እግዚአብሔር ፀጋህ አልጐደለ ለእኔ ለልጅህ ቤትህ ያገባኛል አባብሎ ምህረትህ (፬x)

አዝ አንተን ከአገኘ ሰው ምን ይሆናል (፫x) አንተን ከያዘ ሰው ምን ይሆናል (፫x) የልቤ ማረፊያ ነህ የማምለጫ አለቴ እኮራብሃለሁኝ ኢየሱስ መድሃኒቴ (፪x)

አትለዋወጥ ጠዋት ማታ ፊትህ አይጠቁር የእኔ ጌታ አልቆረቆረኝም ትከሻህ ጌታዬ ተመችተኽኛል አንተ ነህ አለኝታዬ (፬x)

አዝ አንተን ከአገኘ ሰው ምን ይሆናል (፫x) (ኦ ምን ይሆናል) አንተን ከያዘ ሰው ምን ይሆናል (፫x) የልቤ ማረፊያ ነህ የማምለጫ አለቴ እኮራብሃለሁኝ ኢየሱስ መድሃኒቴ (፪x)

ሰማይ ምድርንም ትገዛለህ የፈቀድከውን ታደርጋለህ አንዳች አላጣሁም በስምህ ለምኜ ፊቴ አላፈረም እጅህን ታምኜ (፬x)

አዝ አንተን ከአገኘ ሰው ምን ይሆና (፫x) (ኦ ምን ይሆናል) አንተን ከያዘ ሰው ምን ይሆናል (፫x) የልቤ ማረፊያ ነህ የማምለጫ አለቴ እኮራብሃለሁኝ ኢየሱስ መድሃኒቴ (፪x)