የለህም ፡ እኩያ (Yelehem Ekuya) - ዮሴፍ ፡ በቀለ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሴፍ ፡ በቀለ
(Yoseph Bekele)

Lyrics.jpg


(3)

ስንቱን ፡ ላውራ
(Sentun Lawra)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ በቀለ ፡ አልበሞች
(Albums by Yoseph Bekele)

ሊታይ ፡ በማይቻል ፡ ብርሃን ፡ ውስጥ ፡ አለህ
ከምድር ፡ ጫፍ ፡ እስከጫፍ ፡ ሁሉ ፡ እኮ ፡ ግዛትህ
አለቅነት ፡ ስልጣን ፡ ክብር ፡ የአንተ ፡ ብቻ
እናመልክሃለን ፡ ኢየሱስ ፡ የለህ ፡ ብቻ (፪x)

አዝ፦ ሃሌሉያ (፪x)
ሃሌሉያ ፡ የለህም ፡ እኩያ (፪x)
የለህም ፡ እኩያ (፬x)

ስግደትና ፡ አምልኮ ፡ ለጌታ ፡ ለሰራዊት ፡ ሁሉ ፡ አለቃ
ለሆንከው ፡ አባታችን ፡ ንጉሣችን (ንጉሣችን)
ፈዋሻችን ፡ ነህ ፡ አዳኛችን ፡ ምርኩዛችን ፡ መታመኛችን
እርስታችን ፡ እግዚአብሔር ፡ ሃገራችን (ሃገራችን)
እንገዛልሃለን ፡ ወድቀን ፡ አዲስ ፡ ቅኔን ፡ እየተቀኘን
ክበር ፡ ለዘለዓለም ፡ ንገሥ ፡ ለዘለዓለም ፡ ቅዱስ ፡ አባታችን

ሰማይ ፡ ዙፋንህ ፡ ነው ፡ ምድር ፡ መረገጫህ
ጊዜና ፡ ሁኔታ ፡ ቦታ ፡ አይወስንህ
አሰራርህ ፡ ግሩም ፡ ከአይምሮ ፡ በላይ ፡ ነው
አገዛዝህ ፡ ምቹ ፡ ከማንም ፡ ልዩ ፡ ነው (፪x)

አዝ፦ ሃሌሉያ (፪x)
ሃሌሉያ ፡ የለህም ፡ እኩያ (፪x)
የለህም ፡ እኩያ (፬x)

ስግደትና ፡ አምልኮ ፡ ለጌታ ፡ ለሰራዊት ፡ ሁሉ ፡ አለቃ
ለሆንከው ፡ አባታችን ፡ ንጉሣችን (ንጉሣችን)
ፈዋሻችን ፡ ነህ ፡ አዳኛችን ፡ ምርኩዛችን ፡ መታመኛችን
እርስታችን ፡ እግዚአብሔር ፡ ሃገራችን (ሃገራችን)
እንገዛልሃለን ፡ ወድቀን ፡ አዲስ ፡ ቅኔን ፡ እየተቀኘን
ክበር ፡ ለዘለዓለም ፡ ንገሥ ፡ ለዘለዓለም ፡ ቅዱስ ፡ አባታችን

የጥበብ ፡ ሁሉ ፡ ምንጭ ፡ የዕውቀት ፡ መሰረት
የሰላም ፡ የደስታ ፡ የፍቅር ፡ ተምሳሌት
አንተ ፡ እኮ ፡ ነህ ፡ ጌታ ፡ ለእኛስ ፡ ማረፊያችን
እውነተኛ ፡ ወዳጅ ፡ ብሩኩ ፡ ተስፋችን (፪x)

አዝ፦ ሃሌሉያ (፪x)
ሃሌሉያ ፡ የለህም ፡ እኩያ (፪x)
የለህም ፡ እኩያ (፬x)