አዳኝ ፡ የለም ፡ ከአንተ ፡ ሌላ (Adagn Yelem Keante Liela) - ዮሴፍ ፡ በቀለ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሴፍ ፡ በቀለ
(Yoseph Bekele)

Lyrics.jpg


(2)

ማህተሜን ፡ የፈታህ
(Mahetemien Yefetah)

ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ በቀለ ፡ አልበሞች
(Albums by Yoseph Bekele)

 
አዝ፦ ነፍሴ ፡ ምሥጋናህን ፡ ታመጣለች
አባት ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ የለም ፡ ትላለች
ውለታህ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ የእኔ ፡ ጌታ
ልስገድ ፡ ልገዛልህ ፡ ጥዋት ፡ ማታ
ልስገድ ፡ ልገዛልህ ፡ ጥዋት ፡ ማታ
ጋሻዪ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
በምሥጋና ፡ ሆ ፡ እያልኩኝ
በድል ፡ ዛሬም ፡ እሄዳለሁኝ
ዘምራለሁ ፡ በታላቅ ፡ ዜማ
አዳኝ ፡ የለም ፡ ከአንተ ፡ ሌላ
ከአንተ ፡ ሌላ (፬x)

ማን ፡ አየው ፡ ያንን ፡ ብሶቴን
ማን ፡ ሰማው ፡ ብርቱ ፡ ለቅሶዬን
ጩኸቴን ፡ ሰምተህ ፡ ደረስህ
እምባዬን ፡ ከዐይኔ ፡ አበስህ

እንደአንተ ፡ ያለ ፡ አላየሁም
እንደአንተ ፡ ያለ ፡ አልሰማሁም
ኢየሱሴ ፡ የእኔ ፡ አለኝታ
ክበር ፡ በዕልልታ

ወድሃለሁኝ ፡ ጌታዬ ፡ ወድሃለሁኝ
ወድሃለሁኝ ፡ ኢየሱሴ ፡ ወድሃለሁኝ
ወድሃለሁኝ ፡ አባቴ ፡ ወድሃለሁኝ
ወድሃለሁኝ ፡ ወዳጄ ፡ ወድሃለሁኝ

አዝ፦ ነፍሴ ፡ ምሥጋናህን ፡ ታመጣለች
አባት ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ የለም ፡ ትላለች
ውለታህ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ የእኔ ፡ ጌታ
ልስገድ ፡ ልገዛልህ ፡ ጥዋት ፡ ማታ
ልስገድ ፡ ልገዛልህ ፡ ጥዋት ፡ ማታ
ጋሻዪ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
በምሥጋና ፡ ሆ ፡ እያልኩኝ
በድል ፡ ዛሬም ፡ እሄዳለሁኝ
ዘምራለሁ ፡ በታላቅ ፡ ዜማ
አዳኝ ፡ የለም ፡ ከአንተ ፡ ሌላ
ከአንተ ፡ ሌላ (፬x)

ጓዳዬን ፡ ሁሉ ፡ ታያለህ
በቤቴ ፡ ውስጥ ፡ ትገባለህ
ባጣ ፡ እንኳን ፡ አትርቀኝም
ሰንፈህ ፡ ችላም ፡ አትለኝም
አሳዳጊ ፡ ነህ ፡ መመኪያዬ
ቸር ፡ ወዳጅ ፡ ውዱ ፡ ጌታዬ
አቤት ፡ ኢየሱስ ፡ ምን ፡ ልበልህ
ይባረክ ፡ ስምህ ፡ አዎ

ወድሃለሁኝ ፡ ጌታዬ ፡ ወድሃለሁኝ
ወድሃለሁኝ ፡ ኢየሱሴ ፡ ወድሃለሁኝ
ወድሃለሁኝ ፡ አባቴ ፡ ወድሃለሁኝ
ወድሃለሁኝ ፡ ወዳጄ ፡ ወድሃለሁኝ

አዝ፦ ነፍሴ ፡ ምሥጋናህን ፡ ታመጣለች
አባት ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ የለም ፡ ትላለች
ውለታህ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ የእኔ ፡ ጌታ
ልስገድ ፡ ልገዛልህ ፡ ጥዋት ፡ ማታ
ልስገድ ፡ ልገዛልህ ፡ ጥዋት ፡ ማታ
ጋሻዪ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
በምሥጋና ፡ ሆ ፡ እያልኩኝ
በድል ፡ ዛሬም ፡ እሄዳለሁኝ
ዘምራለሁ ፡ በታላቅ ፡ ዜማ
አዳኝ ፡ የለም ፡ ከአንተ ፡ ሌላ
ከአንተ ፡ ሌላ (፬x)

ብቸኝነት ፡ ሲያስመርረኝ ፡ ባይተዋርነት ፡ ሲያጠቃኝ
ተገን ፡ የሆንከኝ ፡ ረዳቴ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ውዱ ፡ አባቴ
ቀርበኸኝ ፡ በመከራዬ ፡ አገዝከኝ ፡ ጣልከው ፡ ሸክሜን
ወንድም ፡ መከታ ፡ ኢየሱስ ፡ ዘለዓለም ፡ ንገሥ ፡ አዎ

ወድሃለሁኝ ፡ ጌታዬ ፡ ወድሃለሁኝ (ወድሃለሁኝ)
ወድሃለሁኝ ፡ ኢየሱሴ ፡ ወድሃለሁኝ (ኦ ፡ ወድሃለሁኝ)
ወድሃለሁኝ ፡ አባቴ ፡ ወድሃለሁኝ (ወድሃለሁኝ)
ወድሃለሁኝ ፡ ወዳጄ ፡ ወድሃለሁኝ

አዝ፦ ነፍሴ ፡ ምሥጋናህን ፡ ታመጣለች
አባት ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ የለም ፡ ትላለች
ውለታህ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ የእኔ ፡ ጌታ (ልስገድ)
ልስገድ ፡ ልገዛልህ ፡ ጥዋት ፡ ማታ (ልስገድ)
ልስገድ ፡ ልገዛልህ ፡ ጥዋት ፡ ማታ (አሃሃ)
ጋሻዪ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
በምሥጋና ፡ ሆ ፡ እያልኩኝ
በድል ፡ ዛሬም ፡ እሄዳለሁኝ
ዘምራለሁ ፡ በታላቅ ፡ ዜማ
አዳኝ ፡ የለም ፡ ከአንተ ፡ ሌላ
ከአንተ ፡ ሌላ (፬x)