From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ዛሬ ፡ ልጅ ፡ ተብዬ ፡ ክብርን ፡ አግኝቻለሁ
የቀድሞ ፡ ኑሮዬን ፡ ረስቼዋለሁ
ታሪኬን ፡ ለውጠህ ፡ ሰው ፡ አድርጐ ፡ አቆመኝ
የመረጥኩህ ፡ ልጄ ፡ እስራኤል ፡ ሆይ ፡ አለኝ
የመረጥኩህ ፡ ልጄ ፡ የምወድህ ፡ ሆይ ፡ አለኝ
አዝ፦ ኧረ ፡ ይህን ፡ ኢየሱስ ፡ ምን ፡ ብዬ ፡ ልባርከው
ውለታው ፡ በዛብኝ ፡ ከአይምሮዬም ፡ በላይ ፡ ነው
አቤት ፡ ምህረቱ ፡ ምን ፡ እከፍለዋለሁ
እኔም ፡ ክብር ፡ አግኝቼ ፡ አገልጋል ፡ ሆኛለሁ
ይኸው ፡ እድረስልኝ ፡ ዛሬም ፡ ምሥጋናዬ ፡ ኤሄሄ
ማለት ፡ ችያለሁኝ ፡ እኔም ፡ አባብዬ (፪x)
በክርስትናዬ ፡ እድሜን ፡ ቆጥሬያለሁ
በልማዳዊ ፡ ሕይወት ፡ ተመላልሻለሁ
ዛሬ ፡ ግን ፡ ኢየሱስ ፡ ነፍሴ ፡ አወቀችህ
አምላኬ ፡ ጌታዬ ፡ ውዴ ፡ ነህ ፡ አለችህ
አምላኬ ፡ ጌታዬ ፡ አባቴ ፡ አለችህ
አዝ፦ ኧረ ፡ ይህን ፡ ኢየሱስ ፡ ምን ፡ ብዬ ፡ ልባርከው
ውለታው ፡ በዛብኝ ፡ ከአይምሮዬም ፡ በላይ ፡ ነው
አቤት ፡ ምህረቱ ፡ ምን ፡ እከፍለዋለሁ
እኔም ፡ ክብር ፡ አግኝቼ ፡ አገልጋል ፡ ሆኛለሁ
ይኸው ፡ እድረስልኝ ፡ ዛሬም ፡ ምሥጋናዬ ፡ ኤሄሄ
ማለት ፡ ችያለሁኝ ፡ እኔም ፡ አባብዬ (፪x)
የስጋዬን ፡ ሳስብ ፡ እንዲያው ፡ ስቅበዘበዝ
ጠላት ፡ ቤቴ ፡ ገብቶ ፡ ምርኮን ፡ ሲበዘብዝ
እርሱ ፡ ግን ፡ ጌታዬ ፡ አሰበኝ ፡ ለአንድ ፡ አፍታ
ኃይሌም ፡ ተመለሰ ፡ ጠላቴም ፡ ተረታ
ኃይሌም ፡ ተመለሰ ፡ ይክበር ፡ የእኔ ፡ ጌታ
አዝ፦ ኧረ ፡ ይህን ፡ ኢየሱስ ፡ ምን ፡ ብዬ ፡ ልባርከው
ውለታው ፡ በዛብኝ ፡ ከአይምሮዬም ፡ በላይ ፡ ነው
አቤት ፡ ምህረቱ ፡ ምን ፡ እከፍለዋለሁ
እኔም ፡ ክብር ፡ አግኝቼ ፡ አገልጋል ፡ ሆኛለሁ
ይኸው ፡ እድረስልኝ ፡ ዛሬም ፡ ምሥጋናዬ ፡ ኤሄሄ
ማለት ፡ ችያለሁኝ ፡ እኔም ፡ አባብዬ (፪x)
|