From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ሰላሜ (ሰላሜ) ፡ ሰላሜ (ኦ ፡ ሰላሜ)፡ ሰላሜ ፡ አዎን
ኢየሱስ ፡ ሰላሜ (፪x)
ሰላም ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ሰላሜ
ሰላም ፡ የሕይወቴ ፡ ማረፊያ
ሰላም ፡ በአንተ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ሰላም ፡ ሕይወቴ ፡ እኮ ፡ ረካ
ረካ ፡ ረካ ፡ ረካ ፡ አዎ
ባጣ ፡ አይጨንቀኝም ፡ በእርሱ ፡ እጽናናለሁ
ብራብ ፡ አይገደኝም ፡ ክብሩን ፡ ሳይ ፡ እጠግባለሁ
ቢጠማኝም ፡ እንኳ ፡ ፍፁም ፡ እርካታዬ
ኢየሱሴ ፡ ነው ፡ ለእኔስ ፡ የሕይወት ፡ ውሃዬ
አዝ፦ ኢየሱስ ፡ ሰላሜ ፡ ነው ፡ ማን ፡ ይወስድብኛል
ከብርና ፡ ከወርቅ ፡ ሁሉ ፡ ይበልጥብኛል
እርካታ ፡ ለነፍሴ ፡ መጽናኛዬም ፡ እርሱ
ድጋፌ ፡ ምርኩዜ ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ (፫x) ፡ አዎን ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ (፫x) ፡ ጌታ ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
እርሱ ፡ ውበትን ፡ አጥቶ ፡ ውበት ፡ የሆነልኝ
ደም ፡ ግባቱን ፡ አጥቶ ፡ ደም ፡ ግባቱን ፡ ሰጠኝ
በእርሱ ፡ የተነሳ ፡ ሞገስ ፡ አግኝቻለሁ
በተራራ ፡ ጫፍ ፡ ላይ ፡ ቤቴን ፡ መስርቻለሁ
አዝ፦ ኢየሱስ ፡ ሰላሜ ፡ ነው ፡ ማን ፡ ይወስድብኛል
ከብርና ፡ ከወርቅ ፡ ሁሉ ፡ ይበልጥብኛል
እርካታ ፡ ለነፍሴ ፡ መጽናኛዬም ፡ እርሱ
ድጋፌ ፡ ምርኩዜ ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ (፫x) ፡ አዎን ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ (፫x) ፡ ጌታ ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
በብርና ፡ በወርቅ ፡ ወይም ፡ በሃብት ፡ ብዛት
በኃይሌም ፡ አይደለም ፡ ሰላም ፡ ያገኘሁት
ከአብ ፡ ዘንድ ፡ ተልኮ ፡ እኔን ፡ ያሳረፈኝ
ኢየሱሴ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ ሰላሜ ፡ የሆነኝ
አዝ፦ ኢየሱስ ፡ ሰላሜ ፡ ነው ፡ ማን ፡ ይወስድብኛል
ከብርና ፡ ከወርቅ ፡ ሁሉ ፡ ይበልጥብኛል
እርካታ ፡ ለነፍሴ ፡ መጽናኛዬም ፡ እርሱ
ድጋፌ ፡ ምርኩዜ ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ (፫x) ፡ አዎን ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ (፫x) ፡ ጌታ ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ስለ ፡ እኔ ፡ በደል ፡ እርሱ ፡ ተንገላቶ
አሳረፈኝ ፡ ውዴ ፡ አበሳዬን ፡ ወስዶ
ዛሬማ ፡ ኢየሱሴ ፡ ቅርሴ ፡ ሆኖልኛል
በሰማዩ ፡ ስፍራ ፡ በመንፈስ ፡ ባርኮኛል
አዝ፦ ኢየሱስ ፡ ሰላሜ ፡ ነው ፡ ማን ፡ ይወስድብኛል
ከብርና ፡ ከወርቅ ፡ ሁሉ ፡ ይበልጥብኛል
እርካታ ፡ ለነፍሴ ፡ መጽናኛዬም ፡ እርሱ
ድጋፌ ፡ ምርኩዜ ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ (፫x) ፡ አዎን ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ (፫x) ፡ ጌታ ፡ ጋሻዬ ፡ ነው ፡ እርሱ
ማዕበሉ ፡ ቢያናውጥ ፡ ወጀቡ ፡ ቢበዛም
ሁሉ ፡ ባዶ ፡ ቢሆን ፡ ኑሮ ፡ ባይሳካም
እኔስ ፡ አባብዬ ፡ ተንተርሻለሁኝ
ከቶ ፡ አልናወጥም ፡ ተሸሽጌያለሁኝ
ሰላሜ (ሰላሜ) ፡ ሰላሜ (ኦ ፡ ሰላሜ)፡ ሰላሜ ፡ አዎን
ኢየሱስ ፡ ሰላሜ
ሰላም ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ሰላሜ
ሰላም ፡ የሕይወቴ ፡ ማረፊያ
ሰላም ፡ በአንተ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ሰላም ፡ ሕይወቴ ፡ እኮ ፡ ረካ
ረካ ፡ ረካ ፡ ረካ ፡ አዎ
|