From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ውለታህ ፡ አሃሃ ፡ ውለታህ ፡ ብዙ ፡ ብዙ
አንተ ፡ ጌታዬ ፡ ባለውለታዬ (፪x)
ባለውለታዬ ፡ ጌታ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ባለውለታዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ኢየሱሴ ፡ ስለእኔ ፡ ያኔ ፡ የቃተትከው
ከኃጢአት ፡ በሽታ ፡ እኔን ፡ ለማዳን ፡ ነው
በእኔ ፡ ፈንታ ፡ ቆስለህ ፡ እኔን ፡ ፈወስከኝ
ውለታህን ፡ ሳስብ ፡ እጅግ ፡ ደነቀኝ
ተመስገን ፡ አልኩኝ
አዝ፦ ውለታህ ፡ አሃሃ ፡ ውለታህ ፡ ብዙ ፡ ብዙ
አንተ ፡ ጌታዬ ፡ ባለውለታዬ (፪x)
ባለውለታዬ ፡ ጌታ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ባለውለታዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ጠላቴ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ምሽግን ፡ መሽጐ
ነፍሴን ፡ ሊያጠፋት ፡ ወጥመዱን ፡ ዘርግቶ
የጠላቴን ፡ ወጥመድን ፡ ሰበርክልኝና
ዛሬ ፡ ይሄው ፡ አቆምከኝ ፡ በድል ፡ በምሥጋና
መመኪያዬ ፡ ገናና
አዝ፦ ውለታህ ፡ አሃሃ ፡ ውለታህ ፡ ብዙ ፡ ብዙ
አንተ ፡ ጌታዬ ፡ ባለውለታዬ (፪x)
ባለውለታዬ ፡ ጌታ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ባለውለታዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ለነፍሴ ፡ ዋልክላት ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ውለታ
ወደደችህ ፡ ነፍሴም ፡ አመጣች ፡ ስጦታ
እንካ ፡ ተቀበላት ፡ የአፏን ፡ ዝማሬ
ሰው ፡ ሆናለች ፡ በአንተ ፡ አምሮባታል ፡ ዛሬ
ታክብርህ ፡ መድህኔ
አዝ፦ ውለታህ ፡ አሃሃ ፡ ውለታህ ፡ ብዙ ፡ ብዙ
አንተ ፡ ጌታዬ (ኤሄ) ፡ ባለውለታዬ (፪x)
ባለውለታዬ ፡ ጌታ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ባለውለታዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ቀስት ፡ ከሚገትሩ ፡ ያኔ ፡ የታደግካት
ከሚያሳድዷት ፡ ሁሉ ፡ የሰወርካት
ክብሯን ፡ ሁሉ ፡ ጥላ ፡ ታሸበሽባለች
ለአምላኬ ፡ ውለታ ፡ ያንስበታል ፡ እያለች
ትባርክሃለች
አዝ፦ ውለታህ ፡ አሃሃ ፡ ውለታህ ፡ ብዙ ፡ ብዙ
አንተ ፡ ጌታዬ (ኤሄ) ፡ ባለውለታዬ (፪x)
ባለውለታዬ ፡ ጌታ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ባለውለታዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ባለውለታዬ (አሃ)
ባለውለታዬ ፡ እንካ ፡ ምሥጋናዬን (አዎ)
ከክፉ ፡ ፍላጻ ፡ ጋሻ ፡ መከታዬ
መመኪያዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ጥላ ፡ ከለላዬ
ውለታህን ፡ ከቶ ፡ እንዴት ፡ እረሳለሁ
እስከዘለዓለም ፡ እቀኝልሃለሁ
ሌላ ፡ ምን ፡ እላለሁ
አዝ፦ እኔስ ፡ በአንተ ፡ ጌታ ፡ ደስ ፡ ይለኛል ፡ አዎ
ደስ ፡ ይለኛል (እሰይ) ፤ ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ጌት ፡ በማዳንህ ፡ ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ደስ ፡ ይለኛል (እሰይ) ፤ ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ስጠራህ ፡ ወዳጄ (አሃ)
ከተፍ ፡ ትላለህ (እህ)
ቀንበሬን ፡ ሰባብረህ (እህ)
ታሳርፈኛለህ (አዎ)
ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ጠላት ፡ ሲከበኝ ፡ ሲያስፈራራኝ
ተስፋ ፡ ማደርገው ፡ ሲጠፋብኝ
ድቅድቅ ፡ ጨለማ ፡ ዙሪያዬ ፡ ከቦኝ
እማየው ፡ ሁሉ ፡ ሙትኝ ፡ ሲመስለኝ
በጭንቄ ፡ ሰዓት ፡ ደረስክልኝ (አዎ)
ጨለማዬንም ፡ ገፈፍክልኝ (እሰይ)
እጅግ ፡ ደስ ፡ አለኝ ፡ በማዳንህ
ነፍሴ ፡ ሁልጊዜ ፡ አንተን ፡ ትባርክህ
አንተን ፡ ትባርክህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
አንተን ፡ ትባርክህ (አዎ)
አዝ፦ እኔስ ፡ በአንተ ፡ ጌታ ፡ ደስ ፡ ይለኛል ፡ አዎ
ደስ ፡ ይለኛል (እሰይ) ፤ ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ጌታ ፡ በማዳንህ ፡ ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ደስ ፡ ይለኛል (እሰይ) ፤ ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ስጠራህ ፡ ወዳጄ (አሃ)
ከተፍ ፡ ትላለህ (እህ)
ቀንበሬን ፡ ሰባብረህ (እህ)
ታሳርፈኛለህ (አዎ)
ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
በምህረትህና ፡ በቸርነትህ ፡ ዓመታቶችን ፡ ታቀዳጃለህ
ምድረ ፡ በዳውም ፡ ስምህን ፡ ይጠግባል
በበረት ፡ ውሃም ፡ ይጥለቀለቃል
መንጐችህ ፡ ሁሉ ፡ ይደሰታሉ
የአንተን ፡ ማዳን ፡ ያኔ ፡ ያያሉ
አንዴት ፡ ደስ ፡ ያሰኛል ፡ አቤቱ ፡ ስራህ
አንተ ፡ ለሕዝብህ ፡ መልካም ፡ አምላክ ፡ ነህ
መልካም ፡ አምላክ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
መልካም ፡ አምላክ ፡ ነህ (አዎ)
አዝ፦ እኔስ ፡ በአንተ ፡ ጌታ ፡ ደስ ፡ ይለኛል ፡ አዎ
ደስ ፡ ይለኛል (እሰይ) ፤ ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ጌታ ፡ በማዳንህ ፡ ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ደስ ፡ ይለኛል (እሰይ) ፤ ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
ስጠራህ ፡ ወዳጄ (አሃ)
ከተፍ ፡ ትላለህ (እህ)
ቀንበሬን ፡ ሰባብረህ (እህ)
ታሳርፈኛለህ (አዎ)
ደስ ፡ ይለኛል (አዎ)
|