አያለሁ (Ayalehu) - ዮሐንስ ፡ ግርማ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሐንስ ፡ ግርማ
(Yohannes Girma)

Lyrics.jpg


(Volume)

የመድረክ ፡ መዝሙሮች
(Talking Songs)

ዓ.ም. (Year): 2019
ቁጥር (Track):

(1)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሐንስ ፡ ግርማ ፡ አልበሞች
(Albums by Yohannes Girma)

አያለሁ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠውን
በታላቅ ክብር ተንሰራፍቶ ያለውን
ሁሉን የሚገዛውን እግዚአብሄር

አያለሁ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠውን
የነበረ ያለ ደግሞ ሚኖረውን
ሁሉን የሚችለውን እግዚአብሄር አያለሁ

አምላኬ የነበረ ያለ ደግሞም የሚኖር ለዘለዓለም
ብቻውን አምላክ ሌላ የሌለህ ሚስተካከልህ
በሰማያት ተንሰራፍቶ ያለ ሃሌሉያ

ግሩም ነው ድንቅ ነው/4

አቤት አቤት አቤት
አቤት ውበት የአምላኬ
መቅደሱን የሞላው ክብርና ግርማው
ዘምር ዘምር ይላል
ክብር ሳትቆጥብ አብዝተህ ስጥ ይላል

አያለሁ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠውን
በታላቅ ክብር ተንሰራፍቶ ያለውን
ሁሉን የሚገዛውን እግዚአብሄር

አያለሁ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠውን
የነበረ ያለ ደግሞ ሚኖረውን
ሁሉን የሚችለውን እግዚአብሄር አያለሁ

እልፍና አላእፍት መላእክት
በመንቀጥቀጥ የሚሰግዱለት
ኪሩቤል ሱራፌል ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሚሉት
በሰማያት ተንሰራፍቶ ያለ ሃሌሉያ

ግሩም ነው ድንቅ ነው/4

አቤት አቤት አቤት
አቤት ውበት የአምላኬ/2
መቅደሱን የሞላው ክብርና ግርማው
ዘምር ዘምር ይላል
ክብር ሳትቆጥብ አብዝተህ ስጥ ይላል/2

አቤቱ አንተ ከምናውቅህ በላይ ነህ
ስላተ የነገሩን ካስታወቁን በላይ እጅግ ጥልቀት አለህ
አቤቱ አንተ ከምናውቅህ በላይ ነህ
ስላንተ የሰበኩን ካስታወቁን በላይ እጅግ ጥልቀት አለህ

ጥበብህ ማይመረመር
ማስተዋልህ ማይለካ
የሃይልህ ብዛት አይመዘን
የዘላለም አምላክ

ግልበት ሁሉ ሊንበረከክ
ክብርን ሊሰጥ የተገባህ የተገባህ
ምላስ ሁሉ ጌትነትህን
ሊመሰክር የተገባህ የተገባህ