ስትወድ ፡ ብዙ (Setewed Bezu) - ዮሐንስ ፡ ግርማ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሐንስ ፡ ግርማ
(Yohannes Girma)

Yohannes Girma 2.jpg


(2)

እርስቴ ፡ ነህ
(Erestie Neh)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 7:34
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሐንስ ፡ ግርማ ፡ አልበሞች
(Albums by Yohannes Girma)

ስትወድ ፡ ብዙ ፡ ስትምር ፡ ብዙ
ደግነትህ ፡ አበዛዙ
መልካምነትህን ፡ ለእኔ ፡ አልቆጠብከው
ለያንዳንዱ ፡ ነገር ፡ አብዝተህ ፡ አየሁ
ከለመንኩህ ፡ እና ፡ ካሰብኩት ፡ በላይ
ሁሉ ፡ ተከናውኖ ፡ ተደርጎልኝ ፡ ሳይ

ምለውን ፡ አጣሁ ፡ ዝም ፡ አሰኘኝ
የአንት ፡ ስራ ፡ አስደነቀኝ (፪x)

አዝ፦ ከተደረግልኝ ፡ በጎነት ፡ አንዳችም ፡ ለእኔ ፡ ማይገባ ፡ ነበር
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ አርገሃልና ፡ እደነቃለሁ
አብዝቼ ፡ ተመስገን ፡ እላለሁ (፪x)

ኃይሌ ፡ እንዳልል ፡ አይደል ፡ ብዙ
ብልጠት ፡ በዝቶ ፡ አልደርስኩ
ለእኔ ፡ አንተ ፡ በርትተህ ፡ ተናጥቀህልኛል
በርትተህ ፡ ተውግተህ ፡ ምርኮን ፡ በዝብዘሃል

እንካ ፡ ምሥጋናዬን ፡ ላንት ፡ ላብዛ ፡ ላብዛ
ሳልጠግብ ፡ ውዳሴህም ፡ አፌን ፡ ከቶ ፡ አልዝጋ
ወዳጄ ፡ ነህ ፡ የምወድህ
ከሁሉ ፡ በላይ ፡ የማበልጥህ (፪x)

አዝ፦ ከተደረግልኝ ፡ በጎነት ፡ አንዳችም ፡ ለእኔ ፡ ማይገባ ፡ ነበር
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ አርገሃልና ፡ እደነቃለሁ
አብዝቼ ፡ ተመስገን ፡ እላለሁ (፪x)

ሙት ፡ ነበርሁ ፡ የማረባ
ከምንደሬ ፡ ስትገባ
ምን ፡ ነበረኝና ፡ ምኔን ፡ ወዶ ፡ ልበል
የትኛው ፡ እኔነቴ ፡ ለዚ ፡ ሳበው ፡ ልበል
እንዲያው ፡ ቸርነትህ ፡ ያ ፡ ፍቅርህ ፡ ካልሆነ
አይገባኝም ፡ መድሃኒቴ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
የአንተ ፡ ውለታ (፪x)

አዝ፦ ከተደረግልኝ ፡ በጎነት ፡ አንዳችም ፡ ለእኔ ፡ ማይገባ ፡ ነበር
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ አርገሃልና ፡ እደነቃለሁ
አብዝቼ ፡ ተመስገን ፡ እላለሁ (፪x)