From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ከቶውን: በለስ ፡ ባያፍራ
በወይንም ፡ ሃረግ ፡ ላይ ፡ ፍሬ ፡ ባይገኝ
የወይራ ፡ ሥራ ፡ ቢጐድል
እርሾችም ፡ መብልን ፡ ባይሰጡ
እኔ ፡ ግን ፡ በእግዚአብሔር ፡ ደስ ፡ ይለኛል
በመድኃኒቴ ፡ አምላክ ፡ ሃሴት ፡ አደርጋለሁ
ጌታ ፡ እግዚአብሔር ፡ ኃይሌ ፡ ነው
እግሮቼን ፡ እንደ ፡ ዋላ ፡ እግሮች ፡ ያበረታል
በከፍታዎች ፡ ላይ ፡ ያስኬደኛል (፪x)
አምላኬ ፡ ደስታዬ ፡ ደስታዬ ፡ ነህ
ኢየሱሴ ፡ ሙላቴ ፡ እርካታዬ ፡ ነህ (፪x)
በቅተኸኛል ፡ ሌላም ፡ አልፈልግም
ቀረም ፡ የምለው ፡ ነገርም ፡ የለኝ
ታምኜብህ ፡ በሁሉ ፡ ነገሬ
ይዤ ፡ መጣሁ ፡ የከንፈሬን ፡ ፍሬ (፪x)
ምን ፡ ይከብደው ፡ ብዬ ፡ ለየትኛው ፡ ልፍራ
ምን ፡ ያቅተውና ፡ ምኑን ፡ ብዬ ፡ ልፍራ (፪x)
ተራራ ፡ ላይ ፡ ማዳን ፡ የቻለው
ሸለቆው ፡ ውስጥ ፡ ኃይል ፡ የእርሱ ፡ ነው
ሁሉን ፡ 'ሚችል ፡ ሥሙ ፡ ኤልሻዳይ
የእኔ ፡ አምላክ ፡ ያለ ፡ በሰማይ (፪x)
እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ከወዴት ፡ ይገኛል
የሕዝቡ ፡ መከታ ፡ ፅኑ ፡ ጋሻ ፡ ሆኗል (፪x)
መመኪያ ፡ ነው ፡ ለትውልድ ፡ ትምክህት
መጓደጃ ፡ የልጅ ፡ ልጅ ፡ ኩራት
'ሚታመኑት ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ ይላሉ
ለዘለዓለም ፡ ማዳኑን ፡ ያያሉ
ከቶውን ፡ በለስ ፡ ባያፍራ
ከወይንም ፡ ሃረግ ፡ ላይ ፡ ፍሬ ፡ ባይገኝ
የወይራ ፡ ሥራ ፡ ቢጐድል
እርሾችም ፡ መብልን ፡ ባይሰጡ
እኔ ፡ ግን ፡ በእግዚአብሔር ፡ ደስ ፡ ይለኛል
በመድኃኒቴ ፡ አምላክ ፡ ሃሴት ፡ አደርጋለሁ
ጌታ ፡ እግዚአብሔር ፡ ኃይሌ ፡ ነው
እግሮቼን ፡ እንደ ፡ ዋላ ፡ እግሮች ፡ ያበረታ
በከፍታዎች ፡ ላይ ፡ ያስኬደኛል (፪x)
|